የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋን በንግግርና በህግ አግባብ መልስ እንዲያገኝ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ ትቀጥላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ በንግግርና በህግ አግባብ መልስ እንዲያገኝ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል ሲሉ ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቷ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ወደብ እንደሌላት ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን አለባት የሚለው ጉዳይ ዘመን አመጣሽ አጀንዳ አለመሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አመልክተዋል።

ማንንም ሳንጎዳ የኛን ጉዳት መቀነስ እንዳለብን አምናለሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ በመሆኗ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት ተናግረዋል።

በዓለም በወደብ አልባ ሀገራት ልምምድ የሌለ ግፍ በኢትዮጵያ ላይ መፈጸሙንና ይህ ጉዳይ አፋጣኝ መፍትሄ ሊያገኝ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መግለጻቸው አይዘነጋም።

በማብራሪያቸውም፥ የባህር በር ጥያቄን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ኢትዮጵያ በባህር በር ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም እንዳላት ተናግረዋል።

ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ መንገድ ነው ብለውም ነበር።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ #Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026