
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ በንግግርና በህግ አግባብ መልስ እንዲያገኝ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቷ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ወደብ እንደሌላት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን አለባት የሚለው ጉዳይ ዘመን አመጣሽ አጀንዳ አለመሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አመልክተዋል።
ማንንም ሳንጎዳ የኛን ጉዳት መቀነስ እንዳለብን አምናለሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ በመሆኗ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት ተናግረዋል።
በዓለም በወደብ አልባ ሀገራት ልምምድ የሌለ ግፍ በኢትዮጵያ ላይ መፈጸሙንና ይህ ጉዳይ አፋጣኝ መፍትሄ ሊያገኝ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መግለጻቸው አይዘነጋም።
በማብራሪያቸውም፥ የባህር በር ጥያቄን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ኢትዮጵያ በባህር በር ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም እንዳላት ተናግረዋል።
ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ መንገድ ነው ብለውም ነበር።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ #Ethiopia
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026