
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ በንግግርና በህግ አግባብ መልስ እንዲያገኝ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቷ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ወደብ እንደሌላት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን አለባት የሚለው ጉዳይ ዘመን አመጣሽ አጀንዳ አለመሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አመልክተዋል።
ማንንም ሳንጎዳ የኛን ጉዳት መቀነስ እንዳለብን አምናለሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ በመሆኗ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት ተናግረዋል።
በዓለም በወደብ አልባ ሀገራት ልምምድ የሌለ ግፍ በኢትዮጵያ ላይ መፈጸሙንና ይህ ጉዳይ አፋጣኝ መፍትሄ ሊያገኝ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መግለጻቸው አይዘነጋም።
በማብራሪያቸውም፥ የባህር በር ጥያቄን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ኢትዮጵያ በባህር በር ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም እንዳላት ተናግረዋል።
ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ መንገድ ነው ብለውም ነበር።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ #Ethiopia
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026