የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ ነው - ቢሮው

Jun 9, 2025

IDOPRESS

ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።


የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ በምርት ዘመኑ ሰፊ መሬትና የሰው ሃይልን በማቀናጀት በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።


በተያዘው መኸር 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 368 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት የሚያስችል የተቀናጀ የልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።


በእስካሁኑ ሂደትም 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ነው አቶ በሪሶ የገለጹት።


በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን ጠቅሰው ለምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር ስርጭት እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።


ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት አሁን ላይ በትራክተር እየለማ መሆኑንም ተናግረዋል።


በአንዳንድ አካባቢዎች ለደረሱ ሰብሎች የጥበቃና እንክብካቤ ከማድረግ በተጨማሪ የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ብክነትን የሚቀንስ እንዲሆን እገዛና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል የገበያ ጥናት በማካሄድ ከባለሀብቱ ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026