
ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ በምርት ዘመኑ ሰፊ መሬትና የሰው ሃይልን በማቀናጀት በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በተያዘው መኸር 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 368 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት የሚያስችል የተቀናጀ የልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ነው አቶ በሪሶ የገለጹት።
በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን ጠቅሰው ለምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር ስርጭት እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት አሁን ላይ በትራክተር እየለማ መሆኑንም ተናግረዋል።
በአንዳንድ አካባቢዎች ለደረሱ ሰብሎች የጥበቃና እንክብካቤ ከማድረግ በተጨማሪ የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ብክነትን የሚቀንስ እንዲሆን እገዛና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል የገበያ ጥናት በማካሄድ ከባለሀብቱ ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026