
ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ በምርት ዘመኑ ሰፊ መሬትና የሰው ሃይልን በማቀናጀት በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በተያዘው መኸር 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 368 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት የሚያስችል የተቀናጀ የልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ነው አቶ በሪሶ የገለጹት።
በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን ጠቅሰው ለምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር ስርጭት እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት አሁን ላይ በትራክተር እየለማ መሆኑንም ተናግረዋል።
በአንዳንድ አካባቢዎች ለደረሱ ሰብሎች የጥበቃና እንክብካቤ ከማድረግ በተጨማሪ የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ብክነትን የሚቀንስ እንዲሆን እገዛና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል የገበያ ጥናት በማካሄድ ከባለሀብቱ ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026