የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በበጀት አመቱ በአገር-አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ 18 አስገዳጅ ደረጃዎች ጸድቀው ወደ ስራ ገብተዋል

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት አመት በአገር-አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ 18 አስገዳጅ ደረጃዎች ጸድቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩቱት ስራ ከጀመረ ከ50 አመት በላይ ማስቆጠሩን ተናግረዋል፡፡

በእነዚህ አመታት አለም አቀፍ አሰራርን ተከትሎ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ለተለያዩ ምርቶችና አገልግሎቶች ብሔራዊ የጥራት ደረጃዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

እስካሁን ድረስም ከ12 ሺህ በላይ ብሔራዊ የጥራት ደረጃዎችን አዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡

ከነዚህ ደረጃዎች ውስጥ 414 የሚሆኑት የምርትና የአገልግሎት አይነቶች አስገዳጅ ደረጃዎች መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

በሰው ህይወት፣በእንስሳት፣ በእጽዋት፣በአካባቢ እና በብሔራዊ ደህንነት ላይ አደጋ የሚያስከትሉ ምርትና አገልግሎቶች አስገዳጅ ደረጃ እንደሚወጣላቸው ጠቁመዋል፡፡

በ2017 በጀት አመት በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ 18 አስገዳጅ ደረጃዎች ጸድቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡

ኢንስቲቱዩቱ በምርት ጥራት መጓደል የሚከሰቱ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመከላከል በወጪ፣በገቢ እና በአገር ውስጥ ጥቅም ላይ በሚውሉ ምርቶች ላይ የሚለጠፉ የጥራት ደረጃ ምልክቶችን አዘጋጅቶ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡

ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የጥራት ምልክቶቹ ተመሳስለው የሚመረቱ ህገ-ወጥ ምርቶችን ከትክክለኛው ምርት ለመለየት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡

አምራቾች በሚያመርቷቸው ምርቶች ላይ የጥራት ደረጃ ምልክቶችን መጠቀም እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025