አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት አመት በአገር-አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ 18 አስገዳጅ ደረጃዎች ጸድቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩቱት ስራ ከጀመረ ከ50 አመት በላይ ማስቆጠሩን ተናግረዋል፡፡
በእነዚህ አመታት አለም አቀፍ አሰራርን ተከትሎ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ለተለያዩ ምርቶችና አገልግሎቶች ብሔራዊ የጥራት ደረጃዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
እስካሁን ድረስም ከ12 ሺህ በላይ ብሔራዊ የጥራት ደረጃዎችን አዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡
ከነዚህ ደረጃዎች ውስጥ 414 የሚሆኑት የምርትና የአገልግሎት አይነቶች አስገዳጅ ደረጃዎች መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡
በሰው ህይወት፣በእንስሳት፣ በእጽዋት፣በአካባቢ እና በብሔራዊ ደህንነት ላይ አደጋ የሚያስከትሉ ምርትና አገልግሎቶች አስገዳጅ ደረጃ እንደሚወጣላቸው ጠቁመዋል፡፡
በ2017 በጀት አመት በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ 18 አስገዳጅ ደረጃዎች ጸድቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
ኢንስቲቱዩቱ በምርት ጥራት መጓደል የሚከሰቱ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመከላከል በወጪ፣በገቢ እና በአገር ውስጥ ጥቅም ላይ በሚውሉ ምርቶች ላይ የሚለጠፉ የጥራት ደረጃ ምልክቶችን አዘጋጅቶ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡
ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የጥራት ምልክቶቹ ተመሳስለው የሚመረቱ ህገ-ወጥ ምርቶችን ከትክክለኛው ምርት ለመለየት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡
አምራቾች በሚያመርቷቸው ምርቶች ላይ የጥራት ደረጃ ምልክቶችን መጠቀም እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025