የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አቅምን ጥቅም ላይ ለማዋል ዘመኑን የዋጀ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ላይ በትኩረት ይሰራል

Jun 11, 2025

IDOPRESS


አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኢትዮጵያ እምቅ የኢንቨስትመንት አቅምን ጥቅም ላይ ለማዋል ዘመኑን የዋጀ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ላይ ይበልጥ በማተኮር እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ።


የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመሪዎችና ባለሙያዎች ስብሰባ "አዳዲስ መዳረሻዎችን ማሰስ፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አንቀሳቃሽ" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ እንዳሉት፤ መድረኩ ለውጭ ጉዳይ ስራዎች መሰረት የሆነውን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ለማጠናከር ያግዛል።


የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች የተፈጠሩ ምቹ የኢንቨስትመንት እድሎችን ከሀገር ውስጥ ባለፈ የውጭ ኢንቨስተሮች እንዲጠቀሙባቸው የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አቅሞች ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በንግድ ኢንቨስትመንትና በሌሎች ዘርፎች ለማስተሳሰር ጠንካራ ዲፕሎማሲ ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል።


ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ዕምቅ አቅም ለውጭ ባለሀብቶችና ኢንቨስተሮች በሚገባ ማስተዋወቅ የሚያስችል ዘመኑን የዋጀ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እንደሚደረግም ተናግረዋል።


ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው ስኬታማነት የውጭ ባለሀብቶችና ኩባንያዎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ፣ በዚህም በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተፈጠሩ ዕድሎችን በሚገባ ለማሳወቅ ይሰራል ነው ያሉት።


የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማሻገር በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በጸጋዋ ልክ እንድትለማ አቅሟን በማስተዋወቅ ጠንካራ የኢኮኖሚ አጋሮችን መፍጠር ይገባል ብለዋል።


ኮሚሽኑ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አማራጮችን በሚገባ ለማስተዋወቅ "የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ስትራቴጂ" ተግባራዊ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።


አየርላንድ፣ እስራኤል እና ሌሎች የካሪቢያን ሀገሮች የኢንቨስትመንት አቅማቸውን ማሳደግ የቻሉት የተሻሉ ኢንቨስተሮች በመመልመል መሆኑን ገልጸው፣ ኢትዮጵያም በዚህ ላይ ትኩረት ታደርጋለች ብለዋል።


ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተወዳዳሪና ተመራጭ የውጭ ኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን ጠቅሰው፣ ካላት እምቅ አቅም አንፃር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።


የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ቢዝነስ ተኮር ማድረግ የሚያስችል ተሻጋሪ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ዘላቂ ማድረግ የሚያስችል የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መደረጉን ጠቅሰው፣ ለስኬታማነቱ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026