አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በክረምቱ ወቅት የፍራፍሬ ችግኝ በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቡናና ሻይ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒ አሚን እንዳሉት በዘንድሮ የክረምት ወቅት በተለይ በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ተክሎችን ለማልማት ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።
ለዚህም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ምርጥ ዘር በማባዛት በልዩ ሁኔታ በኩታ ገጠም ለማልማት በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በአጠቃላይ በክረምቱ 200 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለማልማት መታቀዱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 5 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሚለማው መሬት 500 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ገልጸው ልማቱም በሰባት ዞኖች ውስጥ በሰፊው እንደሚከናወን ተናግረዋል።
በክረምቱ ወራት የሚተከሉት 12 ዓይነት የፍራፍሬ ችግኞች ሲሆኑ እስካሁንም 450 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
ችግኞቹም በዋናነት አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ብርቱካንን የሚያካትት ሲሆን ልማቱም በጅማ፣ በቡኖ በደሌ፣ በኢሉአባቦር፣ በ አራቱም የወለጋ ዞኖች፣ በጉጂ፣ በቦረና፣ በአርሲና በባሌ እንደሚከናወንም ለማሳያነት ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ጊዜ የመሬት መረጣና ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በአንዳንድ አካባቢዎች ተከላ መጀመሩንም ተናግረዋል።
በክልሉ የፍራፍሬ ልማት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉ ፍራፍሬዎች አሁን ላይ በሀገር ውስጥና በዓለም ገበያ ላይ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘት መጀመሩን ተናግረዋል።
በልማቱ ላይ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂና በአቅርቦት አያያዝ ላይ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው የማይቋረጥ የባለሙያ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸውም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025