የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ በክረምት ወቅት የፍራፍሬ ችግኝ በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም ይለማል

Jun 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በክረምቱ ወቅት የፍራፍሬ ችግኝ በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቡናና ሻይ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒ አሚን እንዳሉት በዘንድሮ የክረምት ወቅት በተለይ በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ተክሎችን ለማልማት ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።

ለዚህም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ምርጥ ዘር በማባዛት በልዩ ሁኔታ በኩታ ገጠም ለማልማት በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


በአጠቃላይ በክረምቱ 200 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለማልማት መታቀዱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 5 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ከሚለማው መሬት 500 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ገልጸው ልማቱም በሰባት ዞኖች ውስጥ በሰፊው እንደሚከናወን ተናግረዋል።

በክረምቱ ወራት የሚተከሉት 12 ዓይነት የፍራፍሬ ችግኞች ሲሆኑ እስካሁንም 450 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።

ችግኞቹም በዋናነት አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ብርቱካንን የሚያካትት ሲሆን ልማቱም በጅማ፣ በቡኖ በደሌ፣ በኢሉአባቦር፣ በ አራቱም የወለጋ ዞኖች፣ በጉጂ፣ በቦረና፣ በአርሲና በባሌ እንደሚከናወንም ለማሳያነት ጠቅሰዋል።


በአሁኑ ጊዜ የመሬት መረጣና ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በአንዳንድ አካባቢዎች ተከላ መጀመሩንም ተናግረዋል።

በክልሉ የፍራፍሬ ልማት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉ ፍራፍሬዎች አሁን ላይ በሀገር ውስጥና በዓለም ገበያ ላይ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘት መጀመሩን ተናግረዋል።

በልማቱ ላይ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂና በአቅርቦት አያያዝ ላይ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው የማይቋረጥ የባለሙያ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸውም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025