ሀዋሳ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባባር በስታስቲክስ መረጃ አያያዝና አመራር ዙሪያ ለክልል ሴክተር አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች በሃዋሳ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጀሚላ መሃመድ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት፥ በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉ አድርጎ መመዝገብ ይገባል፡፡
አስተዳደራዊ መረጃዎች እንደሃገር ያለውን የስታስቲክስ መረጃ ክፍተት የሚሞሉ ቢሆንም በእስካሁኑ ሂደት በተገቢው ባለመደራጀታቸው በተፈለገው ልክ ለስታስቲክስ ዓላማ ያለመዋላቸውን አንስተዋል፡፡
በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ በእቅድ ላይ የተመሰረተ ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የክልሎችን ስታስቲክሳዊ መረጃ አያያዝ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የመሬት ምዝገባ፣የግብርና ግብዓቶች ስርጭት፣የግብር፣ የገበያ ዋጋን ጨምሮ አስተዳደራዊና መሰረታዊ የስነ-ህዝብ መረጃዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመሰብሰብ ወቅታዊ፣ትክክለኛና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን ማቅረብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ቢሮው ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ መረጃዎችን የመሰበሰብ፣ የማደራጀትና የመተንተን ኃላፊነቱን ለመወጣት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የክልሉን የልማት እና እድገት ደረጃን የሚያሳዩ ጥናቶችን በማካሄድ ለፖሊሲ ግብዓት፣ ለእቅድ፣ ለጥናትና ምርምር የሚውሉ ወቅታዊ መረጃዎችን እያደራጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉና ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ እንዲሆኑ የባለሙያውንና የአመራሩን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት የሃዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አሰጋሽ አሰፋ፤ አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በመረጃ አያያዝና አመራር ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከአራቱም ዞኖች ለተውጣጡ አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
ስልጠናውም ለተከታታይ ስድስት ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025