የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ ይገባል-አገልግሎቱ

Jun 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባባር በስታስቲክስ መረጃ አያያዝና አመራር ዙሪያ ለክልል ሴክተር አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች በሃዋሳ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡


የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጀሚላ መሃመድ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት፥ በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉ አድርጎ መመዝገብ ይገባል፡፡

አስተዳደራዊ መረጃዎች እንደሃገር ያለውን የስታስቲክስ መረጃ ክፍተት የሚሞሉ ቢሆንም በእስካሁኑ ሂደት በተገቢው ባለመደራጀታቸው በተፈለገው ልክ ለስታስቲክስ ዓላማ ያለመዋላቸውን አንስተዋል፡፡

በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ በእቅድ ላይ የተመሰረተ ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የክልሎችን ስታስቲክሳዊ መረጃ አያያዝ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የመሬት ምዝገባ፣የግብርና ግብዓቶች ስርጭት፣የግብር፣ የገበያ ዋጋን ጨምሮ አስተዳደራዊና መሰረታዊ የስነ-ህዝብ መረጃዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመሰብሰብ ወቅታዊ፣ትክክለኛና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን ማቅረብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡


የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ቢሮው ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ መረጃዎችን የመሰበሰብ፣ የማደራጀትና የመተንተን ኃላፊነቱን ለመወጣት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም የክልሉን የልማት እና እድገት ደረጃን የሚያሳዩ ጥናቶችን በማካሄድ ለፖሊሲ ግብዓት፣ ለእቅድ፣ ለጥናትና ምርምር የሚውሉ ወቅታዊ መረጃዎችን እያደራጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉና ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ እንዲሆኑ የባለሙያውንና የአመራሩን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት የሃዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አሰጋሽ አሰፋ፤ አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በመረጃ አያያዝና አመራር ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከአራቱም ዞኖች ለተውጣጡ አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

ስልጠናውም ለተከታታይ ስድስት ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026