
ሀዋሳ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባባር በስታስቲክስ መረጃ አያያዝና አመራር ዙሪያ ለክልል ሴክተር አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች በሃዋሳ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጀሚላ መሃመድ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት፥ በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉ አድርጎ መመዝገብ ይገባል፡፡
አስተዳደራዊ መረጃዎች እንደሃገር ያለውን የስታስቲክስ መረጃ ክፍተት የሚሞሉ ቢሆንም በእስካሁኑ ሂደት በተገቢው ባለመደራጀታቸው በተፈለገው ልክ ለስታስቲክስ ዓላማ ያለመዋላቸውን አንስተዋል፡፡
በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ በእቅድ ላይ የተመሰረተ ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የክልሎችን ስታስቲክሳዊ መረጃ አያያዝ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የመሬት ምዝገባ፣የግብርና ግብዓቶች ስርጭት፣የግብር፣ የገበያ ዋጋን ጨምሮ አስተዳደራዊና መሰረታዊ የስነ-ህዝብ መረጃዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመሰብሰብ ወቅታዊ፣ትክክለኛና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን ማቅረብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ቢሮው ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ መረጃዎችን የመሰበሰብ፣ የማደራጀትና የመተንተን ኃላፊነቱን ለመወጣት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የክልሉን የልማት እና እድገት ደረጃን የሚያሳዩ ጥናቶችን በማካሄድ ለፖሊሲ ግብዓት፣ ለእቅድ፣ ለጥናትና ምርምር የሚውሉ ወቅታዊ መረጃዎችን እያደራጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉና ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ እንዲሆኑ የባለሙያውንና የአመራሩን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት የሃዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አሰጋሽ አሰፋ፤ አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በመረጃ አያያዝና አመራር ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከአራቱም ዞኖች ለተውጣጡ አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
ስልጠናውም ለተከታታይ ስድስት ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026