የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ ይገባል-አገልግሎቱ

Jun 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ መዋል እንዲችሉ በአግባቡ መመዝገብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባባር በስታስቲክስ መረጃ አያያዝና አመራር ዙሪያ ለክልል ሴክተር አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች በሃዋሳ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡


የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጀሚላ መሃመድ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት፥ በመንግስት ተቋማት የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉ አድርጎ መመዝገብ ይገባል፡፡

አስተዳደራዊ መረጃዎች እንደሃገር ያለውን የስታስቲክስ መረጃ ክፍተት የሚሞሉ ቢሆንም በእስካሁኑ ሂደት በተገቢው ባለመደራጀታቸው በተፈለገው ልክ ለስታስቲክስ ዓላማ ያለመዋላቸውን አንስተዋል፡፡

በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ በእቅድ ላይ የተመሰረተ ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የክልሎችን ስታስቲክሳዊ መረጃ አያያዝ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የመሬት ምዝገባ፣የግብርና ግብዓቶች ስርጭት፣የግብር፣ የገበያ ዋጋን ጨምሮ አስተዳደራዊና መሰረታዊ የስነ-ህዝብ መረጃዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመሰብሰብ ወቅታዊ፣ትክክለኛና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን ማቅረብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡


የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ቢሮው ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ መረጃዎችን የመሰበሰብ፣ የማደራጀትና የመተንተን ኃላፊነቱን ለመወጣት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም የክልሉን የልማት እና እድገት ደረጃን የሚያሳዩ ጥናቶችን በማካሄድ ለፖሊሲ ግብዓት፣ ለእቅድ፣ ለጥናትና ምርምር የሚውሉ ወቅታዊ መረጃዎችን እያደራጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የሚሰበሰቡ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለስታስቲክስ ዓላማ እንዲውሉና ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ እንዲሆኑ የባለሙያውንና የአመራሩን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት የሃዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አሰጋሽ አሰፋ፤ አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በመረጃ አያያዝና አመራር ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከአራቱም ዞኖች ለተውጣጡ አመራሮችና የመረጃ ባለሙያዎች ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

ስልጠናውም ለተከታታይ ስድስት ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026