የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው - ኮርፖሬሽኑ

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ገለፀ።

ኮርፖሬሽኑ ከናሽናል ኤርዌይስና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን በቀጣይ የርጭት አውሮፕላን አገልግሎት ተደራሽነትን ማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችለውን ውይይት በአዳማ ከተማ አካሂዷል።


የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ፈለቀ ገዛኸኝ በወቅቱ እንደገለፁት የበረሃ አንበጣን ከመከላከል ባለፈ የሰብል ምርትና ምርታማነትን የሚቀንሱ ተባዮች ለማጥፋት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው።

ኮርፖሬሽኑ የራሱ በሆነ 10ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በ22 የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ አሁን ላይ ተጨማሪ 5ሺህ ሄክታር መሬት ወደ እርሻ በማስገባት የተለያዩ የሰብል ምርጥ ዘሮችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር በ6ሺህ ሄክታር ላይ የለሙ የተለያዩ የምርጥ ዘር ሰብሎች በአረም፤ በተባይና በሌሎች ተያያዥ የሰብል በሽታዎች እንዳይጎዱ በአውሮፕላን ርጭት መካሄዱን ለአብነት ጠቅሰዋል።


የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ስራ አስኪያጅ ጫላ አበበ በበኩላቸው ኢንተርፕራይዙ ከ32ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ60 በላይ የሰብል ዝርያዎችን በማልማት የምርጥ ዘር ፍላጎትን ለማሟላት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢንተርፕራይዙ በ2016/17 ምርት ዘመን ከ800ሺህ ኩንታል በላይ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር ማምረቱን ጠቅሰው የፀረ አረምና ፀረ ሰብል በሽታ ማጥፊያ የርጭት አውሮፕላን በመጠቀሙና የሰብል እንክብካቤ ስራ በመስራቱ ከ160ሺህ ኩንታል በላይ ተጨማሪ ምርት ማግኘት መቻሉን አስታውቀዋል።

ድርጅቱ በዋናነት በምስራቅ ባሌና ባሌ፣ በአርሲና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የስንዴ ልማት እንዲሁም በወለጋ በበቆሎ ምርጥ ዘር ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ኢንተርፕራይዙ በተለይ ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር የምርጥ ዘር ብዜት ውጤታማነትን አሁን ካለበት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በ2017/18 የምርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለንን ቅንጅት በማጠናከር ምርታማነትን በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ አቅደን እየሰራን ነው ሲሉም አክለዋል።


የናሽናል ኤርዌይስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የበረሃ አንበጣን ጨምሮ የአውሮፕላን ፀረ ተባይና ፀረ መድኃኒቶች ርጭት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ዕድገት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የማቅረብ ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

በቀጣይም በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር ተፈራርመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025