የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የእንስሳት መኖ እና ሌሎች የግብዓት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jun 20, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ) በሲዳማ ክልል የእንስሳት መኖን ጨምሮ በዘርፉ የሚያጋጥሙ የግብዓት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮ ኃላፊው አቶ ተክሌ ጆምባ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ መኖን ጨምሮ በዘርፉ የግብዓት እጥረት እንዳያጋጥም በእቅድ የታገዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡

በክልሉ ያጋጠመውን የመኖ ዋጋ መናርና አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ አርሶ አደሩ በጓሮ መኖ እንዲያለማ የማድረግና የመኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡

በተያዘው ዓመት በቀን 1 ሺህ 600 ኩንታል የሚያመርት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት ኃላፊው በቀጣዩ በጀት ዓመትም አምስት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንደሚገቡ ገልጸዋል ፡፡

በክልሉ ያለውን የመኖ ተደራሽነት ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍም የህብረት ስራ ማህበራት በየወረዳው በማቋቋም ለአርሶአደሩ እንዲያሰራጩ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በሌላ በኩልም ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር ከሃንጋሪ የመጡ 20 ሺህ ወላጅ ዶሮዎች ከሶስት ወር በኋላ ዝርያቸው የተሻሻሉ የአንድ ቀን ጫጩቶችን መፈልፈል እንደሚጀምሩ ተናግረዋል፡፡

በዚህም በክልሉ ያለውን የአንድ ቀን ጫጩት አቅርቦት ችግር በመቅረፍ እንደ ሃገር በዘርፉ ሞዴል ለመሆን በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የእንስሳት በሽታን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችል የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪ በተያዘው ዓመት መቋቋሙን ኃላፊው ገልፀው በተለያዩ አካባቢዎች የእንስሳት ጤና መከታተያ የህክምና ማእከላትም አገልግሎት መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡

ቢሮው በቀጣይ ዓመት ከሚተገብራቸው በርካታ እቅዶች መካከል በእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ዘርፍ የሚያጋጥሙ የግብዓት እጥረቶችን መቅረፍ ቀዳሚው መሆኑን አቶ ተክሌ ተናግረዋል፡፡

የግብዓት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍም በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቅሰው ለዚህም ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በይርጋለም ከተማ አስተዳደር የሚገኘው ጋኔ የዶሮ እርባታ ኃላፊነቱ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ እንየው ማህበሩ በ5 ሺህ የአንድ ቀን ጫጩት ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል፡፡


በአሁኑ ወቅትም በቀን እስከ 4 ሺህ 500 እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መሆኑን ጠቅሰው ለ30 ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡

10 ሺህ የአንድ ቀን ዶሮ ጫጩቶችን ለመቀበል የቦታ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቅሰው መኖን ጨምሮ የግብዓት እጥረቶች ቢቀረፉ በተሻለ አምርተው የበለጠ ተጠቃሚ መሆን እንደሚሆኑም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025