
ሀዋሳ ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ) በሲዳማ ክልል የእንስሳት መኖን ጨምሮ በዘርፉ የሚያጋጥሙ የግብዓት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮ ኃላፊው አቶ ተክሌ ጆምባ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ መኖን ጨምሮ በዘርፉ የግብዓት እጥረት እንዳያጋጥም በእቅድ የታገዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡
በክልሉ ያጋጠመውን የመኖ ዋጋ መናርና አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ አርሶ አደሩ በጓሮ መኖ እንዲያለማ የማድረግና የመኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡
በተያዘው ዓመት በቀን 1 ሺህ 600 ኩንታል የሚያመርት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት ኃላፊው በቀጣዩ በጀት ዓመትም አምስት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንደሚገቡ ገልጸዋል ፡፡
በክልሉ ያለውን የመኖ ተደራሽነት ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍም የህብረት ስራ ማህበራት በየወረዳው በማቋቋም ለአርሶአደሩ እንዲያሰራጩ ይደረጋል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩልም ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር ከሃንጋሪ የመጡ 20 ሺህ ወላጅ ዶሮዎች ከሶስት ወር በኋላ ዝርያቸው የተሻሻሉ የአንድ ቀን ጫጩቶችን መፈልፈል እንደሚጀምሩ ተናግረዋል፡፡
በዚህም በክልሉ ያለውን የአንድ ቀን ጫጩት አቅርቦት ችግር በመቅረፍ እንደ ሃገር በዘርፉ ሞዴል ለመሆን በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የእንስሳት በሽታን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችል የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪ በተያዘው ዓመት መቋቋሙን ኃላፊው ገልፀው በተለያዩ አካባቢዎች የእንስሳት ጤና መከታተያ የህክምና ማእከላትም አገልግሎት መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
ቢሮው በቀጣይ ዓመት ከሚተገብራቸው በርካታ እቅዶች መካከል በእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ዘርፍ የሚያጋጥሙ የግብዓት እጥረቶችን መቅረፍ ቀዳሚው መሆኑን አቶ ተክሌ ተናግረዋል፡፡
የግብዓት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍም በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቅሰው ለዚህም ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በይርጋለም ከተማ አስተዳደር የሚገኘው ጋኔ የዶሮ እርባታ ኃላፊነቱ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ እንየው ማህበሩ በ5 ሺህ የአንድ ቀን ጫጩት ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅትም በቀን እስከ 4 ሺህ 500 እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መሆኑን ጠቅሰው ለ30 ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡
10 ሺህ የአንድ ቀን ዶሮ ጫጩቶችን ለመቀበል የቦታ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቅሰው መኖን ጨምሮ የግብዓት እጥረቶች ቢቀረፉ በተሻለ አምርተው የበለጠ ተጠቃሚ መሆን እንደሚሆኑም ተናግረዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026