የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሁሉም ዜጎች በእኩል የሚስተናገዱበት አካታች ስርዓት ነው

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሁሉም ዜጎች በእኩል የሚስተናገዱበት አካታች ስርዓት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ ገለጹ።

ከሰኔ 14/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት "የሲቪል ሰርቪስ ተቋማትን ቅልጥፍና እና ጽናትን በማሳደግ በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን መሙላት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የተካሄደው 10ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም ተጠናቋል።


የፎረሙ ማጠቃለያ መርሃ ግብርም የአፍሪካ ሕብረት፣ የአባል ሀገራት የስራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ተካሂዷል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ በዚሁ ወቅት፥ ኢትዮጵያ የህዝብ አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ያከናወነቻቸውን ተግባራት በተሞክሮነት ስታጋራ ክብር ይሰማናል ብለዋል።

የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም የተሰጠው መሪ ቃል የተቋማትን የጋራ ርዕይ እውን ለማድረግ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

በአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የብሔራዊ ቤተ-መንግስት ዕድሳት፣ የሳይንስ ሙዚየም ግንባታ፣ የከተሞች የኮሪደርና የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክቶች እየተሳለጡ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል የህዝብን የአገልግሎት ፍላጎት ያማከለና ሁሉም የዜጎችን በቴክኖሎጂ የተጋዘ፣ በአክብሮትና በኃላፊነት መንፈስ የሚገለገሉበት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ የተሟላ ማዕድ በሚወክለው የመሶብ አገልግሎት በሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በዘመናዊ አገልግሎት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የፎረሙ ተሳታፊዎች የመዲናዋ ጉብኝትም የአፍሪካ ህዝባዊ ተቋማት በአንድ ማዕከል ፍትሕዊና ዘመናዊ አገልግሎትን ለመሻሻል የተደረጉ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአፍሪካ የህዝብ አገልግሎት ቀን መካሄዱም በፍትሕዊነት፣ በዲጂታል ሥርዓት እንዲሁም ብቃት ባላቸው ሰዎች የሚመሩ ስኬታማ ተቋማትን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የሕብረቱ አህጉራዊ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተቃሚነት ለማሻሻል የተደረጉ የፖሊሲ ለውጥ እርምጃዎችን ለማስቀጠል መጠቀም እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያም 10ኛው የአፍሪካ አህጉራዊ የህዝብ አገልግሎት ቀንን በማስተናገዷ ኩራት እንደሚሰማት ገልጸዋል።


በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ በመንግስት አገልግሎታቸው ስኬት ያስመዘገቡ የኢትዮጵያ፣ የኬኒያ፣ የሴኔጋል፣ የደቡብ አፍሪካ፣ የዚምባቡዌ፣ የዛምቢያ እና የካሜሩን ተቋማትና የተቀማት የስራ ኃላፊዎች ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026