
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሁሉም ዜጎች በእኩል የሚስተናገዱበት አካታች ስርዓት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ ገለጹ።
ከሰኔ 14/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት "የሲቪል ሰርቪስ ተቋማትን ቅልጥፍና እና ጽናትን በማሳደግ በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን መሙላት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የተካሄደው 10ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም ተጠናቋል።

የፎረሙ ማጠቃለያ መርሃ ግብርም የአፍሪካ ሕብረት፣ የአባል ሀገራት የስራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ተካሂዷል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ በዚሁ ወቅት፥ ኢትዮጵያ የህዝብ አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ያከናወነቻቸውን ተግባራት በተሞክሮነት ስታጋራ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም የተሰጠው መሪ ቃል የተቋማትን የጋራ ርዕይ እውን ለማድረግ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የብሔራዊ ቤተ-መንግስት ዕድሳት፣ የሳይንስ ሙዚየም ግንባታ፣ የከተሞች የኮሪደርና የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክቶች እየተሳለጡ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
የመሶብ አንድ ማዕከል የህዝብን የአገልግሎት ፍላጎት ያማከለና ሁሉም የዜጎችን በቴክኖሎጂ የተጋዘ፣ በአክብሮትና በኃላፊነት መንፈስ የሚገለገሉበት መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ የተሟላ ማዕድ በሚወክለው የመሶብ አገልግሎት በሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በዘመናዊ አገልግሎት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች የመዲናዋ ጉብኝትም የአፍሪካ ህዝባዊ ተቋማት በአንድ ማዕከል ፍትሕዊና ዘመናዊ አገልግሎትን ለመሻሻል የተደረጉ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የአፍሪካ የህዝብ አገልግሎት ቀን መካሄዱም በፍትሕዊነት፣ በዲጂታል ሥርዓት እንዲሁም ብቃት ባላቸው ሰዎች የሚመሩ ስኬታማ ተቋማትን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
የሕብረቱ አህጉራዊ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፎረም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተቃሚነት ለማሻሻል የተደረጉ የፖሊሲ ለውጥ እርምጃዎችን ለማስቀጠል መጠቀም እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያም 10ኛው የአፍሪካ አህጉራዊ የህዝብ አገልግሎት ቀንን በማስተናገዷ ኩራት እንደሚሰማት ገልጸዋል።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ በመንግስት አገልግሎታቸው ስኬት ያስመዘገቡ የኢትዮጵያ፣ የኬኒያ፣ የሴኔጋል፣ የደቡብ አፍሪካ፣ የዚምባቡዌ፣ የዛምቢያ እና የካሜሩን ተቋማትና የተቀማት የስራ ኃላፊዎች ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026