የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዘንድሮው የመኸር ወቅት እርሻ ውጤታማ ለመሆን ጠንክረን እየሰራን እንገኛለን - አርሶ አደሮች

Jun 25, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦ በዘንድሮው የመኸር ወቅት እርሻ ስራ ውጤታማ ለመሆን ተግተው እየሰሩ መሆናቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤና ጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች ተናገሩ።

በክልሉ ለመኸር እርሻ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በበቂ ሁኔታ እየቀረበ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገልጿል።

በ2017/18 የመኸር ወቅት ከ560 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በመሸፈን ከ54 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱንም አስታውቋል፡፡

ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የስልጤና የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች በ2017/18 የመኸር ወቅት እርሻ ተገቢውን ምርት ለማግኘት መሬትን ደጋግሞ በማረስና በማለስለስ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።


በስልጤ ዞን ምዕራብ አዘርኔት በርበሬ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አብራር ሙስጤና አርሶ አደር አኑዋር ሸምሱ እንዳሉት የበልግ ወቅት ጨርሰው የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ መሬት የማለስለስና ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች እያደረጉ ናቸው፡፡

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጉራጌ ዞን በእኖር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ወልዴ ተክሉ በበኩላቸው በኩታ ገጠም ማሳ ለአምስት ሆነው 10 ሄክታር መሬት በቅንጅት እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በበልግ በቆሎና ጤፍ በማምረት ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው ለመኸርም የተሻለ ውጤት ለማግኘት ማሳቸውን ዝግጁ እያደረጉ መሆኑንና ዘንድሮ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በበቂ ሁኔታ እንደቀረበላቸው ገልጸዋል፡፡

በዞኑ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሀሰን ነስሩ በበኩላቸው ያላቸውን ግማሽ ሄክታር ማሳ በገብስ ለመሸፈን በትራክተር ታግዘው እያረሱ መሆኑን ተናግረዋል።


የወረዳው የግብርና ባለሙያ ነስሮ ሰዒድ የመኸር እርሻን ውጤታማ ማድረግ በሚያስችል መልኩ የግብርና ግብዓት አቅርቦት ማቀላጠፍ ለአርሶ አደሩ ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ የማሳ ዝግጅትና ሌሎች ድጋፎች እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጎደቦ፣ ለበጀት ዓመቱ በዕቅድ ከተያዘው 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ790ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል ብለዋል፡፡


የአርሶ አደሩን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በዘንድሮ ዓመት የግብርና ግብዓት ከሌሎች ጊዜያት በተሻለና በተቀናጀ መልኩ መቅረቡንም አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026