
ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦ በዘንድሮው የመኸር ወቅት እርሻ ስራ ውጤታማ ለመሆን ተግተው እየሰሩ መሆናቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤና ጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች ተናገሩ።
በክልሉ ለመኸር እርሻ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በበቂ ሁኔታ እየቀረበ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገልጿል።
በ2017/18 የመኸር ወቅት ከ560 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በመሸፈን ከ54 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱንም አስታውቋል፡፡
ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የስልጤና የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች በ2017/18 የመኸር ወቅት እርሻ ተገቢውን ምርት ለማግኘት መሬትን ደጋግሞ በማረስና በማለስለስ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በስልጤ ዞን ምዕራብ አዘርኔት በርበሬ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አብራር ሙስጤና አርሶ አደር አኑዋር ሸምሱ እንዳሉት የበልግ ወቅት ጨርሰው የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ መሬት የማለስለስና ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች እያደረጉ ናቸው፡፡
ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጉራጌ ዞን በእኖር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ወልዴ ተክሉ በበኩላቸው በኩታ ገጠም ማሳ ለአምስት ሆነው 10 ሄክታር መሬት በቅንጅት እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በበልግ በቆሎና ጤፍ በማምረት ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው ለመኸርም የተሻለ ውጤት ለማግኘት ማሳቸውን ዝግጁ እያደረጉ መሆኑንና ዘንድሮ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በበቂ ሁኔታ እንደቀረበላቸው ገልጸዋል፡፡
በዞኑ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሀሰን ነስሩ በበኩላቸው ያላቸውን ግማሽ ሄክታር ማሳ በገብስ ለመሸፈን በትራክተር ታግዘው እያረሱ መሆኑን ተናግረዋል።

የወረዳው የግብርና ባለሙያ ነስሮ ሰዒድ የመኸር እርሻን ውጤታማ ማድረግ በሚያስችል መልኩ የግብርና ግብዓት አቅርቦት ማቀላጠፍ ለአርሶ አደሩ ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ የማሳ ዝግጅትና ሌሎች ድጋፎች እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጎደቦ፣ ለበጀት ዓመቱ በዕቅድ ከተያዘው 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ790ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል ብለዋል፡፡

የአርሶ አደሩን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በዘንድሮ ዓመት የግብርና ግብዓት ከሌሎች ጊዜያት በተሻለና በተቀናጀ መልኩ መቅረቡንም አስረድተዋል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026