የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በባሌ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ257 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለምቷል

Jun 25, 2025

IDOPRESS

ሮቤ ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፡-በባሌ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ257 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል ዘሮች መልማቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በባሌ ዞን የበልግ እርሻ ወቅት ከመጋቢት አጋማሽ እስከ ነሐሴ ያለውን ጊዜ የሚያጠቃልል መሆኑ ይታወቃል።

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ደረጀ ግርማ እንዳሉት፣ በዞኑ በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ257 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል ዘሮች ለምቷል።

በዞኑ ከለማው የእርሻ መሬት መካከል ከ70 በመቶ የሚበልጠው የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ በኩታ ገጠም የለማ መሆኑንም አመልክተዋል።


አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ለማረጋገጥ ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ የሀገር ውስጥና የውጪ ገበያ አማራጮችን ጭምር ታሳቢ በማድረግ እንዲያመርት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በበልጉ ወቅት እየለማ ከሚገኘው አጠቃላይ መሬት መካከል ከ40 ሺህ ሄክታር የሚበልጠው ገበያ ተኮር በሆኑ ሰሊጥ፣ ማሾ፣ ቦሎቄና የለውዝ ምርቶች መልማቱን በማሳያነት አንስተዋል።

የዘንድሮ የዝናብ ስርጭት በተለይም በቆላማ አካባቢዎች ጥሩ ስርጭት ስለነበረው ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ መሆኑንና በአርሶ አደሩ እንክብካቤ እየተደረገለት እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ከዋና ዋና ሰብል ልማቱም 8 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ መቀመጡንም ባለሙያው ተናግረዋል።

በዞኑ የሲናና ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙአውያ ፉዓድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በወረዳው በዘንድሮ የበልግ ወቅት 50ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ፣ ገብስና ሌሎች ሰብሎች ለምቷል።


በተለይም በዘንድሮው የበልግ አዝመራ የአርሶ አደሩን የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ይበልጥ ለማሻሻል በተቀመጠው ግብ መሰረት ከአጠቃላይ ልማቱ 60 በመቶ የሚበልጠው መሬት የተሻሻሉ አሰራሮችን በመጠቀም በኩታ ገጠም መልማቱን ተናግረዋል።

በልማቱ እየተሳተፉ ከሚገኙ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ሐሰን አህመድ በሰጡት አስተያየት፣ በባለፈው የመኽር እርሻ ከአንድ ሄክታር መሬት ከ60 ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት መሰብሰባቸውን ተናግረዋል።

በዘንድሮ የበልግ ወቅት የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በመጠቀም የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችል የሰብል እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውንም አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025