
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2017 (ኢዜአ)፦ የ2025 የአፍሪካ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ዘርፍ የአሰራርና ቁጥጥር ስርዓት ደህንነት ጉባዔና ስልጠና ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ገለጸ።
በኮሚሽኑ አዘጋጅነት "ጠንካራ የቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ዘርፍ የአሰራርና የቁጥጥር ሥርዓት ለተረጋጋ የፋይናንስ ተደራሽነት" በሚል መሪ ሀሳብ ለሶስት ቀናት ይካሄዳል ተብሏል።
በጉባኤና በስልጠናው ለሚሳተፉ እንግዶች ዛሬ ማምሻውን በብሔራዊ ቤተ መንግሥት የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ስነ-ስርዓት ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሺፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር)፣የልማት አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ከአፍሪካ 24 አገራት፣ሰሜን አሜሪካና አውሮፓ የሚወከሉ ተሳታፊዎች በሚታደሙበት በዚህ የስልጠና መድረክና ጉባዔ በቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አሰራርና ቁጥጥር ቁልፍ ጉዳዮችና ተግዳሮቶች ላይ ውይይት ይደረጋል።
በማህበራቱ አሰራር ወጥነት፣ግልጸኝነትና አስተማማኝነት ያለው ስርዓት መፍጠር ላይ ያጠነጠነ መሆኑም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሺፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር)፥ ጉባኤውን የአፍሪካ የአንድነትና ትብብር ምልክት በሆነችው አዲስ አበባ ማስተናገድ በመቻላችን ለኢትዮጵያና ለኮሚሽናችን ትልቅ ክብር ነው ብለዋል፡፡
ይህ አህጉራዊ ጉባዔና ስልጠና ለአፍሪካ የኅብረት ሥራ ንቅናቄ በወሳኝ ጊዜ የተዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ዘርፉን ከተለምዷዊ መዋቅር ወደ ዘመናዊ አመራርና አሰራር የሚከተል፣ ተወዳዳሪ ተቋም ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት አወንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።
ኢትዮጵያ የኅብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም በማድረግ ላይ መሆኗንም አንስተዋል።
በመድረኩ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ዘርፍ ህጋዊ ማዕቀፍ ለማሻሻል እያከናወነች ያለውን የሪፎርም ስራዎች ይቀርባሉ ብለዋል።
መድረኩ አዳዲስ ሀሳቦች ለመለዋወጥ፣ ውጤታማ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ለመጠቀምና ከአፍሪካ ሀገራት ጋር አጋርነት ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል፡፡
የቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ የአሰራር ደንብ ማዕቀፍን ለማጠናከር፣ አዳዲስ የፋይናንስ አሰራር ስርዓት ለመፍጠርና የቁጥጥርና ክትትል ስርዓትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ አጋዥ እንደሚሆንም ጠቁመዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026