
አዳማ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ) የጤፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት በመጨመር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።
በጤፍ ሰብል ልማትና እሴት ጨምሮ ማምረት ላይ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።
በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ለኢዜአ እንደገለጹት በኢትዮጵያ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች በጤፍ ልማት ላይ ተሰማርተዋል።
እነዚህን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ የጤፍን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ እሴት ጨምሮ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ጤፍን የኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርት ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ኢሳያስ፤ "የጤፍ ምርታማነት አናሳ መሆን፣ የምርጥ ዘርና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክፍተት የዘርፉ ማነቆዎች ናቸው ብለዋል።
በዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ረዳት ተወካይ ወርክቾ ጃተኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በጤፍ ልማት ላይ የጥናትና ምርምር ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
በጤፍ ምርትና ምርታማነት ላይ የሚደረግ ምርምር በሚፈለገው ደረጃ ያለመሆንና ጤፍን በሜካናይዜሽን ግብርና ለማልማት የማሽነሪዎች እጥረት መኖር በጥናት መለየቱን ገልጸዋል።

"የአንድ ሀገር ተቀዳሚ ምርት" የሚል ፕሮጀክት በመቅረጽ በጤፍ ምርት ላይ የምርምርና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የጤፍ ሰብል ከፍተኛ ተመራማሪ ሀብቴ ጁፋር (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የጤፍ ምርትና ምርታማነት ማነቆዎችን ለመፍታት ከግብርና ሚኒስቴርና ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል።

በዚህም በጤፍ ዝርያ ማሻሻል፣ በተመራማሪዎች አቅም ግንባታ እንዲሁም በጤፍ ምርትና ምርታማነት የባለድርሻ አካላት ፕላት ፎርምን ጭምር በማዘጋጀት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026