
አዳማ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ) የጤፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት በመጨመር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።
በጤፍ ሰብል ልማትና እሴት ጨምሮ ማምረት ላይ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።
በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ለኢዜአ እንደገለጹት በኢትዮጵያ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች በጤፍ ልማት ላይ ተሰማርተዋል።
እነዚህን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ የጤፍን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ እሴት ጨምሮ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ጤፍን የኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርት ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ኢሳያስ፤ "የጤፍ ምርታማነት አናሳ መሆን፣ የምርጥ ዘርና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክፍተት የዘርፉ ማነቆዎች ናቸው ብለዋል።
በዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ረዳት ተወካይ ወርክቾ ጃተኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በጤፍ ልማት ላይ የጥናትና ምርምር ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
በጤፍ ምርትና ምርታማነት ላይ የሚደረግ ምርምር በሚፈለገው ደረጃ ያለመሆንና ጤፍን በሜካናይዜሽን ግብርና ለማልማት የማሽነሪዎች እጥረት መኖር በጥናት መለየቱን ገልጸዋል።

"የአንድ ሀገር ተቀዳሚ ምርት" የሚል ፕሮጀክት በመቅረጽ በጤፍ ምርት ላይ የምርምርና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የጤፍ ሰብል ከፍተኛ ተመራማሪ ሀብቴ ጁፋር (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የጤፍ ምርትና ምርታማነት ማነቆዎችን ለመፍታት ከግብርና ሚኒስቴርና ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል።

በዚህም በጤፍ ዝርያ ማሻሻል፣ በተመራማሪዎች አቅም ግንባታ እንዲሁም በጤፍ ምርትና ምርታማነት የባለድርሻ አካላት ፕላት ፎርምን ጭምር በማዘጋጀት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026