
አዲስ አበባ፤ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የስልጠና አካዳሚ ለበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚ ተመራጭ የስልጠና ማዕከል እየሆነ እንደሚገኝ የኤር ናቪጌሽን ሬጉሌሽን አገልግሎት ዳይሬክተር እና የአካዳሚው ተጠባባቂ ዳይሬክተር ልዑልሰገድ ጉልላት ገለጹ።
ዳይሬክተሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ አካዳሚው ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውጤታማነት ባለሙያዎችን በማፍራት ላይ ይገኛል ብለዋል።
ለበርካታ ዓመታት በአየር ትራፊክ ቁጥጥር፣ በኮሙኒኬሽን እና ናቪጌሽን ሰርቪላንስ (CNC) ዘርፍ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ብቁ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን በማሰማራት ላይ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በዚህ ዓመት ብቻ ከ86 በላይ ባለሙያዎችን በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ወደ ሥራ ማስገባቱን አንስተዋል።
አካዳሚው የሚሰጠው ስልጠና ከሀገር አልፎ ለጎረቤት ሀገራትና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ውጤታማ ስልጠና እየሰጠ ተፈላጊነቱን እያሳደገ ይገኛል ብለዋል።
በቅርቡ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ እንዲሁም ከኮሞሮሶና ሌሎች ሀገራት የመጡ የአቪዬሽን ሰልጣኞችን ማሰልጠኑን ተናግረዋል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን የስልጠና አካዳሚ ሙያተኞቻቸውን ለማሰልጠን ጥያቄ እያቀረቡ እና ተመራጭ እያደረጉት መሆኑን ተናግረዋል።
አካዳሚው በአፍሪካ ትልቅ ስምና ተቀባይነት እንዳለው በማንሳት፥ ይበልጥ ቀጣናውን ለማስተሳሰር በርካታ ተግባራትን በትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በአካዳሚው አሰልጣኝ እና ዋና የአየር ተቆጣጣሪ ቤተልሔም ሞላ በበኩላቸው፥ ስልጠናው የዓለም አቪዬሽን ኢንዱስትሪ በደረሰበት ደረጃ ልክ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በተግባር እና በንድፈ ሀሳብ የተደገፈው ስልጠና ሰልጣኞች ተግባራዊ የሆነ በቂ እውቀት የሚያገኙበት እና በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውጤታማ የሚያደርጋቸው ነው ብለዋል።
ባለፉት ሰባት ወራት በብቁ አሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና መውሰዱን የገለጸልን ደግሞ ከድሬዳዋ የመጣው ምንተስኖት አለማየሁ ነው።

በአቪዬሽን ዘርፉ በተሰማራበት ሙያ ለማገልገል ካለው ተነሳሽነት በተጨማሪ፥ በስልጠናው ያገኘው እውቀት ትልቅ አቅም እንደፈጠረለትም ተናግሯል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026