የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመች

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ የገንዘብ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

ስምምነቱ የቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የእዳ ሽግሽግ (G20 Common Framework debt treatment) አማካኝነት የተፈረመ ነው።

የገንዘብ ሚኒስቴር ስምምነቱን አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ መግባቢያ ሰነዱ እ.አ.አ በማርች 2025 በመርህ ደረጃ የተደረሰውን የብድር ሽግሽግ (Debt treatment) በይፋ ተግባራዊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጿል።

ይህም ለኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አመልክቷል።

ስምምነቱ ለአመታት ሲደረግ ለነበረው ድርድር ስኬታማ መቋጫ ከመሆኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የመንግስት እዳ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።

ኢትዮጵያ የአበዳሪዎች ኮሚቴ አባላትን፣ በተለይም የኢትዮጵያን የዕዳ ሽግሽግ ጥረት በማገዝ ላሳዩት ጽኑ ድጋፍና ትብብር የኮሚቴው የጋራ ሰብሳቢዎች ለሆኑት ቻይና እና ፈረንሳይ ልባዊ ምስጋናዋን አቅርባለች።

የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ በኋላ ስምምነቱ ከእያንዳንዱ የኮሚቴው አባላት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች አማካኝነት ተግባራዊ እንደሚሆን መግለጫው አመላክቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ስምምነቱን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት በእስከ አሁኑ ሂደት የተንጸባረቀው የትብብር መንፈስ በሁለትዮሽ ስምምነቶች ሂደት ወቅትም እንደሚቀጥል እንዲሁም ሂደቱን ለማፋጠን እንደሚረዳ የጸና እምነት አለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከውጭ አበዳሪዎች ጋር በትብብር መስራቷን ትቀጥላለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ከሀገሪቱ የዕዳ ሽግሽግ ፍላጎት እና ሁሉንም አበዳሪዎችን በተነጻጻሪ መንገድ ከማስተናገድ መርህ (Comparability of Treatment) ጋር በሚጣጣም መልኩ ስምምነቶችን ለመፈፀም እንደምትሰራ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪ ኮሚቴው ጋር የተደረሰውን መግባቢያ፣ የቦንድ ባለቤቶችን ጨምሮ ከሌሎች የውጭ አበዳሪዎች ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ የምታደርገውን ጥረት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ነው ያመለከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025