የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመች

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ የገንዘብ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

ስምምነቱ የቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የእዳ ሽግሽግ (G20 Common Framework debt treatment) አማካኝነት የተፈረመ ነው።

የገንዘብ ሚኒስቴር ስምምነቱን አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ መግባቢያ ሰነዱ እ.አ.አ በማርች 2025 በመርህ ደረጃ የተደረሰውን የብድር ሽግሽግ (Debt treatment) በይፋ ተግባራዊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጿል።

ይህም ለኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አመልክቷል።

ስምምነቱ ለአመታት ሲደረግ ለነበረው ድርድር ስኬታማ መቋጫ ከመሆኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የመንግስት እዳ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።

ኢትዮጵያ የአበዳሪዎች ኮሚቴ አባላትን፣ በተለይም የኢትዮጵያን የዕዳ ሽግሽግ ጥረት በማገዝ ላሳዩት ጽኑ ድጋፍና ትብብር የኮሚቴው የጋራ ሰብሳቢዎች ለሆኑት ቻይና እና ፈረንሳይ ልባዊ ምስጋናዋን አቅርባለች።

የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ በኋላ ስምምነቱ ከእያንዳንዱ የኮሚቴው አባላት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች አማካኝነት ተግባራዊ እንደሚሆን መግለጫው አመላክቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ስምምነቱን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት በእስከ አሁኑ ሂደት የተንጸባረቀው የትብብር መንፈስ በሁለትዮሽ ስምምነቶች ሂደት ወቅትም እንደሚቀጥል እንዲሁም ሂደቱን ለማፋጠን እንደሚረዳ የጸና እምነት አለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከውጭ አበዳሪዎች ጋር በትብብር መስራቷን ትቀጥላለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ከሀገሪቱ የዕዳ ሽግሽግ ፍላጎት እና ሁሉንም አበዳሪዎችን በተነጻጻሪ መንገድ ከማስተናገድ መርህ (Comparability of Treatment) ጋር በሚጣጣም መልኩ ስምምነቶችን ለመፈፀም እንደምትሰራ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪ ኮሚቴው ጋር የተደረሰውን መግባቢያ፣ የቦንድ ባለቤቶችን ጨምሮ ከሌሎች የውጭ አበዳሪዎች ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ የምታደርገውን ጥረት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ነው ያመለከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026