
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ የገንዘብ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ስምምነቱ የቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የእዳ ሽግሽግ (G20 Common Framework debt treatment) አማካኝነት የተፈረመ ነው።
የገንዘብ ሚኒስቴር ስምምነቱን አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ መግባቢያ ሰነዱ እ.አ.አ በማርች 2025 በመርህ ደረጃ የተደረሰውን የብድር ሽግሽግ (Debt treatment) በይፋ ተግባራዊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጿል።
ይህም ለኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አመልክቷል።
ስምምነቱ ለአመታት ሲደረግ ለነበረው ድርድር ስኬታማ መቋጫ ከመሆኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የመንግስት እዳ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።
ኢትዮጵያ የአበዳሪዎች ኮሚቴ አባላትን፣ በተለይም የኢትዮጵያን የዕዳ ሽግሽግ ጥረት በማገዝ ላሳዩት ጽኑ ድጋፍና ትብብር የኮሚቴው የጋራ ሰብሳቢዎች ለሆኑት ቻይና እና ፈረንሳይ ልባዊ ምስጋናዋን አቅርባለች።
የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ በኋላ ስምምነቱ ከእያንዳንዱ የኮሚቴው አባላት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች አማካኝነት ተግባራዊ እንደሚሆን መግለጫው አመላክቷል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ስምምነቱን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት በእስከ አሁኑ ሂደት የተንጸባረቀው የትብብር መንፈስ በሁለትዮሽ ስምምነቶች ሂደት ወቅትም እንደሚቀጥል እንዲሁም ሂደቱን ለማፋጠን እንደሚረዳ የጸና እምነት አለን ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከውጭ አበዳሪዎች ጋር በትብብር መስራቷን ትቀጥላለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ከሀገሪቱ የዕዳ ሽግሽግ ፍላጎት እና ሁሉንም አበዳሪዎችን በተነጻጻሪ መንገድ ከማስተናገድ መርህ (Comparability of Treatment) ጋር በሚጣጣም መልኩ ስምምነቶችን ለመፈፀም እንደምትሰራ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪ ኮሚቴው ጋር የተደረሰውን መግባቢያ፣ የቦንድ ባለቤቶችን ጨምሮ ከሌሎች የውጭ አበዳሪዎች ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ የምታደርገውን ጥረት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ነው ያመለከቱት።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026