🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ሳምንት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ማድረግ እንደምትጀምር የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ ከንግድ ቀጣናነት ባለፈ የአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና ለማረጋገጥ ወሳኝ እንደሆነ ይታመናል።
የንግድ ቀጣና ስምምነቱ አፍሪካዊያንን የኢኮኖሚ በማስተሳሰር ፈጣንና ወደ ብልፅግና የሚያሻግር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማረጋገጥ ያስችላል።
የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ድህነትን ለመቀነስ ወሳኝ እንደሆነም ይገለጻል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ለዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ የተደረገውን ስድስተኛ ዙር የሥራ ቡድን ስብሰባ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ በመግለጫቸው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን መጀመር የሚያስችል የሰነድ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በመጭው ሳምንት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ በይፋ እንደምትጀምር አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026