🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የገጠርና ከተማ ሽግግርን በማሳለጥ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እየጣለ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባውን የብራውን ፉድ የበቆሎ፣ ብቅልና አልሚ ምግብ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ከፍተዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን እያሳደገ ነው።
ከለውጡ በፊት በደብረ ብርሃንና ሰሜን ሸዋ ዞን 18 ኢንዱስትሪዎች ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው፤ በአሁኑ ወቅት በደብረ ብርሃን ከተማ መካከለኛና ዝቅተኛ ኢንዱስትሪዎች 105 እንዲሁም በሰሜን ሸዋ ዞን 87 መድረሳቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በየዓመቱም በአማካይ 24 መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እየገቡ መሆኑን አንስተዋል።
በአማራ ክልል የተቀጣጠለው የኢንዱስትሪ አብዮት የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ ነው ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ምርታማነት ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባሻገር የሉዓላዊነትና ራስን የመቻል የኢትዮጵያ ብልጽግና ማብሰሪያ መሆኑንም ተናግረዋል።
መንግስት የዘርፉን ማንሰራራት የሚያጎሉ የፖሊሲ፣ የአደረጃጀት፣ የግብዓት፣ የመሠረተ ልማት፣ የፋይናንስና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያዎች ማድረጉንም አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አምራች ኢንዱስትሪ የገጠርና ከተማ ሽግግርን በማሳለጥ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እየጣለ ነው።
የብራውን ፉድ ፋብሪካም የሚጠቀመው የአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ኩንታል የበቆሎ ግብዓት የገጠርና ከተማ ሽግግርን ለማሳለጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ፋብሪካው በየዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች አስተማማኝ የገበያ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ አቅም እንዳለውም ገልጸዋል።
በዚህም የአርሶ አደሩን ገቢና ኑሮ በማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማሳለጥ እንደሚረዳ አብራርተዋል።
የፋብሪካው ምርትም የቢራ አምራቾችን የብቅል አቅርቦት ፍላጎት ለማሟላት በሚደረገው ጥረት ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል ያሉት ሚኒስትሩ ፤ በምርት አቅርቦት ቅብብሎሽ ውስጥ ያሉ ተዋናዮች እና የኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026