🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የገጠርና ከተማ ሽግግርን በማሳለጥ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እየጣለ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባውን የብራውን ፉድ የበቆሎ፣ ብቅልና አልሚ ምግብ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ከፍተዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን እያሳደገ ነው።
ከለውጡ በፊት በደብረ ብርሃንና ሰሜን ሸዋ ዞን 18 ኢንዱስትሪዎች ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው፤ በአሁኑ ወቅት በደብረ ብርሃን ከተማ መካከለኛና ዝቅተኛ ኢንዱስትሪዎች 105 እንዲሁም በሰሜን ሸዋ ዞን 87 መድረሳቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በየዓመቱም በአማካይ 24 መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እየገቡ መሆኑን አንስተዋል።
በአማራ ክልል የተቀጣጠለው የኢንዱስትሪ አብዮት የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ ነው ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ምርታማነት ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባሻገር የሉዓላዊነትና ራስን የመቻል የኢትዮጵያ ብልጽግና ማብሰሪያ መሆኑንም ተናግረዋል።
መንግስት የዘርፉን ማንሰራራት የሚያጎሉ የፖሊሲ፣ የአደረጃጀት፣ የግብዓት፣ የመሠረተ ልማት፣ የፋይናንስና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያዎች ማድረጉንም አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አምራች ኢንዱስትሪ የገጠርና ከተማ ሽግግርን በማሳለጥ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እየጣለ ነው።
የብራውን ፉድ ፋብሪካም የሚጠቀመው የአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ኩንታል የበቆሎ ግብዓት የገጠርና ከተማ ሽግግርን ለማሳለጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ፋብሪካው በየዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች አስተማማኝ የገበያ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ አቅም እንዳለውም ገልጸዋል።
በዚህም የአርሶ አደሩን ገቢና ኑሮ በማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማሳለጥ እንደሚረዳ አብራርተዋል።
የፋብሪካው ምርትም የቢራ አምራቾችን የብቅል አቅርቦት ፍላጎት ለማሟላት በሚደረገው ጥረት ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል ያሉት ሚኒስትሩ ፤ በምርት አቅርቦት ቅብብሎሽ ውስጥ ያሉ ተዋናዮች እና የኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026