🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶችን አስቀድሞ ለመመከት የሚያስችል ጠንካራአቅም በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
ባንኩ የሳይበር ደህንነት ወርን ለሁለተኛ ጊዜ እያከበረ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪውቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት ትልቅ ትኩረት ሰጥቷል።
ይህን ተከትሎም ባንኩ የ(2020 - 2025) የመጀመሪያ ምዕራፍ ዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቆ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ዲጂታል መር ስትራቴጂ (2025-2030) መሸጋገሩን ገልፀዋል።

አሁን ላይ ከባንኩ ጠቅላላ ግብይት ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ የሚከናወነው በዲጂታል መንገድ መሆኑን ጠቅሰው፤ የግብይት ስርዓቱን ደህንነት ለማስጠበቅ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንM አረጋግጠዋል።
አቶ ኤፍሬም አክለውም የሳይበር ደህንነት አስተዳደርን እስከ ምክትል ፕሬዝዳንት ደረጃ በማሳደግ ባንኩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፋይናንስ ተቋም መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም የሳይበር ደህንነት ክፍሎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ.አይ) የሚሠራ የዜሮ ትረስት ደህንነት ስትራቴጂ (Al-powered Zero Trust Security Strategy) መዘጋጀቱን አመልክተዋል።
የሳይበር ጥቃትን መከላከል የአንድ አካል ብቻ ተግባር አለመሆኑን ጠቁመውም፤ የሚመለከታቸው አካላት ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026