🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ እና ይበልጥ ጠንካራ የሚሆንበት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።
ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ታሪካዊ ወዳጅነትና ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

የሀገራቱ ግንኙነት በዲፕሎማሲ ትስስርና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ(ናም) እና የደቡብ ደቡብ ትብብር ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ላይ የተመሰረተ እንደሆነም ተናግረዋል።
ማሌዥያን በጎበኙበት ወቅት የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ላደረጉላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበው ሁለቱ መሪዎች በሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር ላይ ግልጽ የሆነ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።
ጉብኝቱ ለሀገራቱ ወዳጅነትና ትብብር አዲስ በር የከፈተ መሆኑን ገልጸው በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይትም በተለያዩ መስኮች ያለውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ዕድል መፍጠሩን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ሊያጎልብቱ በሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች መዳሰሳቸውን ነው ያብራሩት።
የኢትዮጵያ እና ማሌዥያ መጻኢ ጊዜ ብሩህ እና ጠንካራ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ያሉ ሲሆን ቀሪ ቆይታቸው ፍሬያማ እንዲሆንም ተመኝተውላቸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025