የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ እና ይበልጥ ጠንካራ የሚሆንበት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።

ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ታሪካዊ ወዳጅነትና ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።


የሀገራቱ ግንኙነት በዲፕሎማሲ ትስስርና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ(ናም) እና የደቡብ ደቡብ ትብብር ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ላይ የተመሰረተ እንደሆነም ተናግረዋል።

ማሌዥያን በጎበኙበት ወቅት የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ላደረጉላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበው ሁለቱ መሪዎች በሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር ላይ ግልጽ የሆነ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።

ጉብኝቱ ለሀገራቱ ወዳጅነትና ትብብር አዲስ በር የከፈተ መሆኑን ገልጸው በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይትም በተለያዩ መስኮች ያለውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ዕድል መፍጠሩን አንስተዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ሊያጎልብቱ በሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች መዳሰሳቸውን ነው ያብራሩት።

የኢትዮጵያ እና ማሌዥያ መጻኢ ጊዜ ብሩህ እና ጠንካራ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ያሉ ሲሆን ቀሪ ቆይታቸው ፍሬያማ እንዲሆንም ተመኝተውላቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026