የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ የጋራ አጀንዳችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ የጋራ አጀንዳችን ነው ሲሉ የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ፣ የብሔራዊ ደሕንነት፣ የቀጣናዊ ልማት ትስስር ብሎም የሀገር ሕልውና ጉዳይ ነው።

ጥያቄው ታሪካዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው በመሆኑ ምላሽ ይሰጠው ዘንድ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በሐረሪ ክልልና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ሕልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ የጋራ አጀንዳችን ነው ብለዋል።

የድሬዳዋ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የድሬዳዋ ሐረር የኢትዮዽያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) አስተባባሪ ዮናስ በትሩ፤ በመልክአ ምድርም ይሁን በታሪክ ኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር የተነጠለ ሕይወት ሊኖራት አይችልም ነው ያሉት።

በመሆኑም የኢትዮዽያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከሕልውና ጋር የተያያዘ እንዲሁም እውነታን የያዘ በመሆኑ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር አጥታ በቆየችባቸው ዓመታት ብዙ ዋጋ መክፈሏን ያነሱት አቶ ዮናስ፤ አሁን ላይ የትውልድ ጥያቄ እና የሀገር ሕልውና ጉዳይ ሆኖ መምጣቱን ገልጸው፤ ምላሽ ሊያገኝ ግድ መሆኑን ገልጸዋል።

የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ሕልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ሁላችንንም ይመለከተናል ነው ያሉት።


የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አስተባባሪ አብዱልሃፊዝ አሕመድ፤ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ የሚሻ የትውልዱ ጥያቄ ነው ብለዋል።

በዚህ ረገድ ፓርቲያቸው ጠንካራ አቋም ያለው መሆኑን አንስተው፤ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

የትውልድ ጥያቄ የሆነውን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የሁላችንም ስራ ሆኖ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026