የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በገቢ አሰባሰብ ሂደት ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት የማዋል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከአማራ ክልል ምክር ቤት ጋር በመተባበር በሚሻሻሉ የገቢ አዋጆች ዙሪያ ዛሬ በደሴ ከተማ መክሯል።


በመድረኩ ላይ የቢሮው ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው።

ለዚህም ከግብር ከፋዩ ማሕበረሰብ ጋር በመወያየት፣ ህገ ወጥ ተግባራትን በመከላከል፣ ገቢ አሰባሰቡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የክልሉን ገቢ ለማሳደግና ወጪን በራስ አቅም ለመሸፈን ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።

የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያ፣ የግብርና ሥራዎች ግብር፣ የቴምብር ቀረጥ ክፍያ እና የኤክሳይዝ ታክስን የተመለከቱ አዋጆችን በማሻሻል የገቢ አቅምን ማጠናከርም እንዲሁ።

በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ድረስ ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አውስተው፤ ቀሪውን በቀጣይ ለመሰብሰብ የተጠናከረ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በገቢ አሰባሰብ ሂደት ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት የማዋል ተግባሩም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መንገሻ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።


በአማራ ክልል ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው፤ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሥርዓት መተግበር እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለረጅም ጊዜ ሲሰራባቸው የነበሩ አዋጆችን ለማሻሻል፣ አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ለማስፋትና ገቢን በፍትሀዊነት ለመሰብሰብ እየተከናወነ ያለው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የደሴ ከተማ ሴት ነጋዴዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ እፀገነት ታደሰ ፤ የንግዱ ማሕበረሰብ በሰራው ልክ ግብሩን እንዲከፍል በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት፣ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ አርሶ አደሮችና የሕግ ምሁራን ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025