የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ግንቦት 28/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።

በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በኢኖቬሽን ዘርፍ የተቀረፁ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መተግበር የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዳዲስ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተመርቆ ስራ ጀምሯል።


ዩኒቨርሲቲው የማእከሉን ተልአኮና አላማ ማሳካት እንዲቻል ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ፊርማም ዛሬ አከናውኗል፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል።

ኢኖቬሽንን ከማበረታታትና ከመደገፍ አንጻር ለፈጠራ ሃሳቦችና ስታርታፖች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር ከምርምርና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቁርኝት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ የማህበረሰቡን ችግር በመፍታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ልማት ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ እንደሚገባም አመልክተዋል።

ከዚህ አንጻር ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ በማተኮር እያከናወናቸው የሚገኙ የምርምር ተግባራት ሞዴል መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል የፈጠራ ሃሳቦች በልጽገው ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡


የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው ማእከሉ የምርምር ሃሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን በመቀበል ሃሳባቸውን ወደ መሬት የሚያወርዱበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ ይፈጥራል ብለዋል፡፡

ዩኒቨርሰቲው ማእከሉን በቴክኖሎጂ፣ በባለሙያዎችና በዘመናዊ መሳሪያዎች በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን ጠቁመው ስራ ፈጣሪዎች ምርምርና የፈጠራ ሃሳባቸው አድጎ ወደ ገበያ እንዲወጣ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡

ማእከሉ ችግር ፈቺ የምርምር ሃሳቦች ከመደርደሪያ ወርደው ወደ ኢንዱስትሪዎችና ካምፓኒዎች እንዲሸጋገሩ ብሎም የማህበረሰቡን ችግር መፍታት እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር በመግለጽ።

በማእከሉ የምረቃ ስነ ስርአት ላይ የአፍሪካ ልህቀት ማእከል ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብረሃን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026