🔇Unmute
ሀዋሳ፣ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፡-የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ ለሪፎርም ሥራዎች ትኩረት መስጠቱን የሲዳማ ክልል ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዓላማ ላይ ለባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በሃዋሳ ከተማ ተካሂዷል።

የቢሮው ሀላፊ አቶ ሀይሌ ሀርሲሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በቢሮው የመንግስት አገልግሎትን ቀልጣፋ፣ ተደራሽና ፍትሀዊ ለማድረግ የአስተዳደር ሪፎርም ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ነው።
የሪፎርም ሥራው የበጀት ሥራዎችን በቴክኖሎጂ ተደግፎ ለማከናወን ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
ቢሮው የክፍያ ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ የሚከናወንበትን አሰራር በመዘርጋት አገልግሎቱን ከጥሬ ገንዝብ ንክኪ ነጻ በማድረግ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት የማስፈን ሥራ መጀመሩንም ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል ገንዘብ ቢሮ የሪፎርም ቴክኒክ ቡድን አስተባባሪ አቶ ጌቱ በቀለ በበኩላቸው እንዳሉት በቢሮው ቀደም ሲል ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች በሪፎርሙ ደረጃ ወጥቶላቸው እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ሪፎርሙ የተቋሙን አሰራር እና የሠራተኛውን የመፈጸም አቅም በማሳደግ የህዝብ ተቀባይነትና አመኔታን ለመፍጠር የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ በገንዘብ ሚኒስቴር የሪፎርም ድጋፍ ቡድን ሀላፊ አቶ ይገዙ ዳባ ናቸው።

ተግባራዊ የሚደረገው የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026