የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብን ተግባራዊ በማድረግ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት ትኩረት ተደርጓል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ዘመናዊ የግብር አሰባሰብን ተግባራዊ በማድረግ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ትኩረት መደረጉ ተገለፀ።

በክልሉ ውስጥ የገቢ አቅምን በማሳደግ የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል።

የገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግም የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን እንደተቻለ ተመላክቷል።

በክልሉ ገቢዎች ቢሮ የግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ታዘባቸው ጣሴ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የህግ ተገዥነትን በማሳደግና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በዚህ በጀት ዓመት ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።

እስከ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ድረስ በተቀናጀ መንገድ በተሰበሰበ ገቢም የዕቅዱን ከ73 በመቶ በላይ ማከናወን እንደተቻለ አመልክተዋል።

የተሰበሰበው ገቢም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ28 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው አስረድተዋል።

ተጨማሪ ገቢው የተገኘው ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከርና በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትልና ቁጥጥር በመደረጉ መሆኑን አንስተዋል።

እንዲሁም ከዚህ ቀደም በግብር ስርዓቱ ውስጥ ያልነበሩ ግብር ከፋዮችን ወደ ግብር ስርዓቱ ማስገባት በመቻሉ መሆኑንም አክለዋል።

በሌላ በኩል በ259 የታክስ ማዕከላት የተቀናጀ የመንግስት የግብር አስተዳደር ስርዓት ተደራሽነትን በማሳደግ የተሟላ አገልግሎት ማቅረብ እንደተቻለ አመልክተዋል።

በግብር አሰባሰብ ሂደቱ ቅሬታ ላቀረቡ 46 ሺህ 285 ግብር ከፋዮች ያቀረቡትን ቅሬታ በመመርመር አፋጣኝ ውሳኔ መስጠት መቻሉንም ገልፀዋል።

በተቋሙ ውስጥ የስነ ምግባር መጓደል የተስተዋለባቸው ባለሙያዎች ላይ ከስራ እስከ ማሰናበት የሚያደርስ ቅጣት መወሰኑን አብራርተዋል።

በቀጣይም የግብር አሰባሰብ አሰራሩን በማዘመን ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ርብርብ ይደረጋል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026