የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኦሮሚያ ክልል በ240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ እየለማ ነው

Jun 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በ240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ 29 ሚሊዮን ኩንታል የፍራፍሬ ምርት መመረቱም ተገልጿል።

በኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ቻላቸው አዱኛ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ለፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ምቹ የአየር ንብረት፣ በቂ የዝናብ መጠንና ተስማሚ የአፈር ዓይነት ያለው በመሆኑ ለዘርፉ ምርታማነት ከፍተኛ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል።

በተለይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የምግብ ስርዓትን ከማሻሻል ረገድ ሚናው የላቀ በመሆኑ በተሰሩት በርካታ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣ በዚህም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ ነው ብለዋል።

ይህንን ተከትሎ እንደ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ማንጎ፣ ብርቱካን፣ አፕል እና ሎሚ ያሉ ዋና ዋና የፍራፍሬ ዓይነቶች የዞኖቹን መልክዓ ምድርና የአየር ንብረት መሰረት በማድረግ በትኩረት እየለማ ነው ብለዋል።

ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ምርጥ ዘሮችን በመጠቀምና የማስፈጸም አቅምን በማሻሻል ልማቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በዚህም በ2013 ዓ.ም ከ90 ሺህ ሄክታር ያልበለጠ የነበረው የፍራፍሬ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየለማ መሆኑን ተናግረዋል።

ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ 29 ሚሊዮን ኩንታል የፍራፍሬ ምርት መመረቱንም ተናግርዋል።

ከዚህ ውስጥም ከ8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የሚሆነው የአቮካዶ ምርት መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት 2 ሺህ 400 ኩንታል የአቮካዶ ምርት ወደ ውጭ መላኩን አንስተው፣ ዘንድሮም በተሻለ ሁኔታ ለመላክ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

አርሶ አደሮቹ የግብርና ኤክስቴንሽን ፓኬጁን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲያደርጉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎችና ስልጠናዎች እየተሰጧቸው መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026