🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የታክስ አሰራርን በማዘመን ፍትሐዊነትና የሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የአስረጂ መድረክ ተካሂዷል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቃዱ ሆረታ በዚህ ወቅት፤ የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ ዘመናዊ የታክስ አሰራር ለመፍጠር ያስቻላል ብለዋል።
በታክስ ከፋዩ ማህበረሰቡ የሚነሱ መሰረታዊ የፍትሐዊና የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችንም መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
የመንግሥትን ገቢ የመሰብሰብ አቅም በማጎልበት ተጠያቂነትን ከግልጸኝነት ያጣመረ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚያስችልም ተናግረዋል።
የምክር ቤቱ አባላትና የሕግ ማዕከል ባለሙያዎችም፤ በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የታክስ ስሌት፣ የይርጋ ጊዜ ገደብ፣ የታክስ ከፋይ መስተንግዶና ተያያዥ ጉዳዮችን በማስመልከት ጥያቄ አንስተዋል።
በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሕግ አማካሪ ዋሲሁን አባተ፤ በረቂቅ አዋጁ የይርጋ ጊዜው አስር ዓመት ሆኖ መቀመጡ በታክስ ከፋዩ ላይ የሚኖረውን ጫና መቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
በገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፈ ተወዳጅ መሐመድ፤ የታክስ ደረሰኝ አለመስጠት ተመሳሳይ የገንዘብ ቅጣት መጣሉ ሆን ተብሎ የሚፈጸምን የታክስ ማጭበርበር በማስቀረትና ደረሰኝ መቁረጥን ባህል ያደርጋል ብለዋል።
በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አማካሪ ያሬድ ፍቃደ በበኩላቸው፤ የገለልተኛ አስማሚ ስርዓት ገለልተኛ ሆኖ የሚቋቋም በመሆኑ ግብር ከፋዩ የሚገጥመውን ችግር መፍቻ ተጨማሪ አማራጭ ነው ብለዋል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ኢኮኖሚው በሚያመነጨው ልክ ገቢን ለመሰብሰብና የታክስ አስተዳደርን ለማዘመን እንደሚያስችል ተናግረዋል።
በአስረጂ መድረኩ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ይበልጥ ማጥራት የሚያስችል ማብራሪያ መሰጠቱን ጠቁመው የተደረጉት ማሻሻያዎች ፍትሐዊነትንና የሕግ ተገዢነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026