የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ህዝቡ በመቅረቡ የመሰረተ ልማት ችግሮች በህዝብ ተሳትፎ ለመፍታት እያስቻለ ነው

Jun 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፣ ሰኔ 4 /2018 (ኢዜአ):- በባሌ ዞን መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ወደ ህዝቡ በመቅረቡ የመሰረተ ልማት ችግሮች በህዝብ ተሳትፎ ለመፍታት እያስቻለ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተዘርግቶ ህዝቡ መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እያገኘ መሆኑ ይታወቃል።

በባሌ ዞን የተዘረጋው የቀበሌ አደረጃጀትም የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ የመሰረተ ልማት ችግሮች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲፈቱ ዕድል መፍጠሩን የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።

በብልጽግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ አፍራሳ እንደገለጹት፤ የቀበሌ አደረጃጀቱ የህብረተሰቡን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ የመሰረተ ልማት ችግሮች እንዲፈቱ ዕድል እየፈጠረ ነው።

ይህ አደረጃጀት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር፣ የአገልግሎትና የልማት ጥያቄዎችን በቅርበት ለመመለስ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል።

ከዚህ በፊት ህብረተሰቡ ከፍትህና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማስጨረስ ወደ ወረዳና ዞን ማዕከላት በመመላለስ ለአላስፈላጊ ወጪና ለስራ ጊዜ መባከን ይዳረግ ነበር ያሉት ኃላፊው፤ በአዲሱ አደረጃጀት እነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ከማግኘታቸውም በላይ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ለማፋጠን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።

በዚህም በህዝብ ተሳትፎ እንዲሁም በመንግስት አቅም የቀበሌ ጽሕፈት ቤቶች ግንባታን ጨምሮ የትምህርት ቤቶች፣ የመንገድና የድልድይ መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ መሆኑን በአብነት አንስተዋል።

የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሀሰን በበኩላቸው፤ አዲሱ አደረጃጀት የወረዳውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በቅርበት ለመመለስ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህዝቡ ተሳትፎ የተሰሩ የድልድይ፣ የመንገድ፣ ሼዶችና የቀበሌ ጽህፈት ቤቶች ግንባታ ሥራዎችም የአደረጃጀቱ ውጤቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አስተያየታቸውን ከሰጡ የወረዳው ነዋሪዎች መካከል አቶ በከር ሱልጣን፤ የቀበሌ አደረጃጀቱ የአካባቢውን ህብረተሰብ የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎች በቅርበት እንዲመለሱ እያገዘ መሆኑን ገልጸው፣ በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡትን ድልድይና የወጣቶች መስሪያ ሼድ በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

ሌላው የወረዳው ነዋሪ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው፤ የቀበሌ አደረጃጀቱ በአካባቢያቸው ተግባራዊ መደረጉ ከዚህ በፊት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት ያስቀረና በልማት ላይ የሚያደርጉትን ተሳትፎ ያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል።

በባሌ ዞን በአጠቃላይ 189 አዲስ የተደራጁ ቀበሌዎች የሚገኙ ሲሆን፣ በእነዚህ ቀበሌዎች የተሟላ የሰው ኃይል ተመድቦ ለማህበረሰቡ በቅርበት አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026