🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለመኸር ሰብል ልማት ከ3 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ ሙሽራ ሲሳይ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ በ2018/2019 የምርት ዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ ግብዓትን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ የማቅረብ ሥራ እየተሰራ ነው።
ለምርት ዘመኑ 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እስካሁን ከ4 ሚሊዮን 822 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያን ወደ ክልሉ በማጓጓዝ ለአርሶ አደሩ የማሰራጨት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
እስካሁንም ከ3 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ የሚሆነው እንደተሰራጨ የገለጹት ዳይሬክተሯ፤ የማዳበሪያ አቅርቦቱ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በምርት ዘመኑ 220 ሺህ ኩንታል የተለያዩ የሰብል ምርጥ ዘር ለማቅረብ በታቀደው መሰረት እስካሁን 137 ሺህ 675 ኩንታል ለአርሶ አደሩ ደርሷል ብለዋል።
የማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦቱ በወቅቱ መካሄዱ አርሶ አደሩ ምርታማነቱን በማሳደግ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባሻገር ለገበያ የሚተርፍ ምርት በአይነት፣ በብዛትና በጥራት እንዲያመርት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክተዋል።
"በመኸር ምርቱ ምንም አይነት የግብዓት አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም እየተሰራ ነው" ያሉት ወይዘሮ ሙሽራ፣ አስፈላጊውን ግብአት ለማቅረብ በየደረጃው በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣ ወረዳ ማይነት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ንጋቴ ጎሸ እንደገለጹት ለዘር የሚያስፈልጋቸውን አምስት ኩንታል ማዳበሪያ ቀድሞ ማግኘታቸው የዘር ሥራቸውን ያለምንም ችግር ለማከናወን አግዟቸዋል።
በሰሜን ጎጃም ዞን የሰሜን ሜጫ ወረዳ እንጉቲ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ስሜነህ አበረ በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የግብርና ግብዓት አቅርቦት ወቅቱን ጠብቆ መከናወኑን ተናግረዋል።
ይህም የዘር ሥራቸውን ፈጥነው በማከናወን የተሻለ ምርት እንዲያገኙ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ነው ያስታወቁት።
በአማራ ክልል በመኸር ወቅት 5 ነጥ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ከ205 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደስራ መገባቱን ከቢሮው የተገ መረጃ ያስረዳል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026