🔇Unmute
ደብረ ብርሃን፤ ሰኔ 7/2018 (ኢዜአ)፡- በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ ከተሞችን የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የተሰራው ስራ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማሳደጉ ተመላከተ።
በዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የመሰረተ ልማት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ አንተነህ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ከተሞች እየተገነባ ያለው የኮሪደር ልማት የኢንዱስትሪ፣ ኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲፋጠን አድርጓል።
በዚህም በዞኑ የሚገኘውን ማዕድንና ሌሎች ጸጋዎች በማልማት ለአገር እድገትና ለህዝብ ዘላቂ ጥቅም ለማዋል ማስቻሉን ገልጸዋል።
ባለፈው ዓመት በሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር የተጀመረውን የኮሪደር ልማት በማስቀጠል ዘንድሮ በዓለም ከተማ፣ በአጣዬ፣ በአረርቲና በለሚ ከተሞች የማስፋት ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።
የኮሪደር ልማቱ የእግረኛ፣ የተሽከርካሪና የሳይክል መንገድን፣ የመብራት፣ የውሃና የቴሌኮም መስመር ዝርጋታንና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን አካቶ እየተገነባ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ለከተሞቹ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትና ገጽታ መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በከተሞቹ ከ81 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የኮብል ስቶን፣ የጠጠር መንገድ ግንባታና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችን በመገንባት ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026