የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 8 ሺህ 961 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 8 ሺህ 961 ኪሎ ግራም ወርቅ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ሀገሪቱ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከወርቅ ማዕድን ዘርፍ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ታሪካዊ ገቢ ማስመዝገቧን ይፋ አድርገዋል።

መንግስት ህገ-ወጥ የወርቅ ዝውውርና ኮንትሮባንድን በመከላከልና አምራቾችን በማበረታታት የወርቅ ግዥ ሥርዓትና የዋጋ ማሻሻያ ማድረጉ ይታወሳል።

በማዕድን ዘርፍ የተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ እና ድጋፍ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ማስቻሉንም አስታውሰዋል።

የማዕድን ሀብት ክምችት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች አንዱ የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ከለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት የማዕድን ምርት ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል።

የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ናስር ሙሐመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ የሰጠው ትኩረት ዘርፉ የሀገር ኢኮኖሚ በመደገፍ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጥር አስችሎታል።

በክልሉ ወርቅን ጨምሮ በርካታ ማዕድናትን በማልማት የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገለጹት ኃላፊው፤ ክልሉ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢም በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን አስታውቀዋል።

ለአብነትም በ2018 በጀት ዓመት 8 ሺሕ 961 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መግባቱን ገልጸው፤ ለስኬቱም መንግሥት በዘርፉ የወሰደው የፖሊሲ ማሻሻያ ለአምራቾች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ ቀጥተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል።

ዘርፉ ለክልሉ የገቢ አቅም መጠናከር ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን እና በበጀት ዓመቱ ቢሮው ከ246 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ከዘርፉ ማግኘቱን ገልጸዋል።

በክልሉ በተለይም አነስተኛ የወርቅ አምራቾች ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወርቅን በዘመናዊ መልኩ ማምረት ከጀመሩ ወዲህ በዘርፉ የሚታየው ውጤት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።

በክልሉ ከወርቅ በተጨማሪ ግራናይት፣ ድንጋይ ከሰል፣ እምነበረድ እና ሌሎች ማዕድናትን ለማልማት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን አበርክቶ አጠናክሮ በማስቀጠል ሁሉንም ማዕድናት ጥቅም ላይ ማዋል ይገባል ብለዋል።

በዘርፉ የሚሠማሩ ወጣቶችም በተግባር የታገዘ ስልጠና ወስደው የማዕድን ስረው ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ ውጤታማ ስራ በመከናወን ላይ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026