🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ ሀምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ስራ መጀመር ለከተማዋ ንግድና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ከቀናት በፊት መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የአየር ትራንስፖርት አገልግሎቱ ተመርቆ ስራ መጀመርን ተከትሎ ኢዜአ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ተመስገን ተድላ ጋር ቆይታ አድርጓል።
በቆይታቸውም የአየር ትራንስፖርት አገልግሎቱ ስራ መጀመር በተለይም ኢንቨስትመንትን ከማጠናከር አንፃር ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ለባለሃብቶች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ጊዜያቸውን በመቆጠብ እና በልማቱ ስኬታማ ከመሆን ባሻገረ ለፈጣንና ቀልጣፋ የገበያ እንቅስቃሴ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ስራ መጀመር ለከተማዋ ንግድና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
በደብረ ማርቆስና አካባቢው ለኢንቨስትመንት ሰፊ እድሎች መኖራቸውን ያነሱት ኃላፊው ባለሃብቶች ይህንን እድል እንዲጠቀሙም ጥሪ አቅርበዋል።

በከተማዋ በተለያዩ ስራዎች ላይ ተሰማርተው ከሚገኙ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ታመነች ታደለ፣ አቶ ነብዩ ብርሃኑ እና ወጣት ተጎዳን ፈጠነ፤ የረጅም ዓመታት ጥያቄያችን ተመልሶ ኤርፖርቱ ስራ በመጀመሩ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል።
የአውሮፕላን ማረፊያው ስራ መጀመር የኢንቨስትመንትና ንግድን በማነቃቃት አዳዲስ የስራ እድል እንዲከፈት የሚያደርግ ነው ብለዋል።

የኤርፖርቱ መገንባት ከአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ባለፈ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት መሳለጥም ትልቅ አቅም መሆኑን አንስተዋል።
የደብረ ማርቆስ ኤርፖርት መሰረተ ልማት ግንባታ ጥያቄ የ30 ዓመታት የአካባቢው ህብረተሰብ ጥያቄ የነበረ ሲሆን በለውጡ መንግስት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ምላሽ ያገኘ መሆኑ ይታወቃል።
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026