🔇Unmute
ጎንደር፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞች መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመገንባት የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸ።
በክልሉ በተለይም በከተሞች የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል የሚያስችል የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

በዚህ የልማት ጥረት ውስጥ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በጡብ ማምረት ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ስልጠና በጎንደር ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ፤ ኮሌጆቹ ቴክኖሎጅን የመቅዳት፣ የማላመድና የመፍጠር አቅማቸውን በመጠቀም የቤት ግንባታ ፕሮጀክት እቅዱ እንዲሳካ መስራት አለባቸው ብለዋል።
በዘመናዊ መንገድ ጡብ በማምረት በከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ውብና ማራኪ ቤቶችን መገንባት አለብን ያሉት አቶ ሽቤ፤ ለዜህም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ከፍተኛ ሚና እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
የዚህ ስልጠና ዋነኛ ዓላማም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ለእቅዱ መሳካት የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል።
የስልጠናው ተሳታፊዎችም ለልማት ፕሮጀክቱ ስኬት የበኩላቸውን ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶችን ለመገንባት እቅድ መያዙን መግለፃቸው ይታወቃል።
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026