የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ከተሞች መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመገንባት የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞች መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመገንባት የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸ።

በክልሉ በተለይም በከተሞች የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል የሚያስችል የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።


በዚህ የልማት ጥረት ውስጥ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በጡብ ማምረት ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ስልጠና በጎንደር ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ፤ ኮሌጆቹ ቴክኖሎጅን የመቅዳት፣ የማላመድና የመፍጠር አቅማቸውን በመጠቀም የቤት ግንባታ ፕሮጀክት እቅዱ እንዲሳካ መስራት አለባቸው ብለዋል።

በዘመናዊ መንገድ ጡብ በማምረት በከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ውብና ማራኪ ቤቶችን መገንባት አለብን ያሉት አቶ ሽቤ፤ ለዜህም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ከፍተኛ ሚና እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የዚህ ስልጠና ዋነኛ ዓላማም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ለእቅዱ መሳካት የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎችም ለልማት ፕሮጀክቱ ስኬት የበኩላቸውን ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶችን ለመገንባት እቅድ መያዙን መግለፃቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026