የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የአማራ ክልል ሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Aug 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የአማራ ክልል ሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ባደረጉት ቆይታ በለውጡ ዓመታት በአማራ ክልል የተከናወኑ የልማት ስራዎችን አስመልከተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው እንደገለጹት፤ በለውጡ ማግስት ከአማራ ክልል ሕዝብ ጋር በተደረጉ ውይይቶች የፍትሐዊ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄ በዋናነት ከተነሱ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነበር።

በወቅቱ የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ በተካሄደው ጥናትም ክልሉ የሚገባውን ያህል ተጠቃሚ እንዳልነበረ መረጋገጡንና ይህም በክልሉ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ዘላቂ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ማነቆ እንደነበር አብራርተዋል።

ባለፉት ዓመታት የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው ለአብነትም ለ18 ዓመታት ግንባታው ሳይጠናቀቅ የቆየውን የመገጭ የመስኖ ፕሮጀክት በርካታ ሀብት በመመደብ ግንባታውን ወደ መገባደድ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ለግድቦች ግንባታ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በመመደብ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አክለዋል።

በግብርናው ዘርፍ በለውጡ ማግስት 90 ሚሊዮን ኩንታል ገደማ የነበረው የክልሉ ዓመታዊ ምርት፣ ምርታማነትን ለማሳደግ በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች አሁን ላይ ከ205 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማድረስ መቻሉን ጠቁመዋል።

በኢንዱስትሪው ዘርፍ ደግሞ ከለውጡ በኋላ የባሕር ዳር፣ የደብረ ብርሃን እና የአረርቲ ኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ፣ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ እንዲሁም በርካታ ሌሎች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ነው ያብራሩት።

ከቱሪዝም አንጻርም የላሊበላ እና የአጼ ፋሲለደስ ቤተ መንግስት እድሳቶች፣ የሎጎ ሐይቅ እና የፈለገ ግዮን ሪዞርት እንዲሁም የጎርጎራ ፕሮጀክት በቱሪዝም ዘርፍ የክልሉን ተጠቃሚነት ያሳደጉ ዋና ዋና ስራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

የመሠረተ ልማት ግንባታን በተመለከተም የነበረው 2000 ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን አሁን ወደ 4ሺህ 500 ኪሎ ሜትር ማደጉን አንስተዋል።

የባሕር ዳር እና የኮምቦልቻ የአየር መንገድ ተርሚናሎችን ጨምሮ በትራንስፖርት ዘርፉ የተለያዩ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም በክልሉ የኤሌክትሪክ ሽፋን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ከነበረበት 20 በመቶ ወደ 40 በመቶ ሽፋን ማሳደግ መቻሉን ጠቁመው ይህ በቂ ባለመሆኑ በቀጣይ የበለጠ ይሰራል ነው ያሉት።

በኮሪደር ልማት ፕሮጀክትም እንዲሁ በክልሉ በሚገኙ 32 ከተሞች በተሰራ የኮሪደር ልማት የከተሞቹ ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እና የአኗኗር ዘይቤ እንዲቀየር አስችሏል ነው ያሉት በማብራሪያቸው።

በዲጂታል ኢኮኖሚው ዘርፍም በ«አምስት ሚሊዮን ኮደርስ» ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በክልሉ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎችን ማሰልጠን መቻሉንም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፉት ዓመታት ልዩ ልዩ ፈተናዎችና እንቅፋቶች ቢኖሩም በክልሉ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በዲጂታል ኢኮኖሚ፣ በመሰረተ ልማት፣ በትምህርት፣ በጤና እና በመጠጥ ውሃ ዘርፎች አመርቂ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል የሕዝቡ የመልማትና የመጠቀም ጥያቄዎች በተሟላ ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026

የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር ያስችላል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...

Jul 7, 2026