የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማኅበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው

Aug 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ ፤ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለፀ።

በቢሮው "አንድነት ለፅዳት፣ ትጋት ለአገልግሎት፣ ውሳኔ ለልማት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የሴክተሩ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ ተካሄዷል።


በወቅቱም የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል እንዳሉት በክልሉ የማኅበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው።

በዚህም ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው በኮሪደር ልማትና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን ረገድ የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የስልጤ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱልሰመድ አብደላ በበኩላቸው በዞኑ ዘመናዊና የተሳለጠ አገልግሎቶችን በመስጠት የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማት ሥራ ከተሞችን ምቹ፣ ፅዱና ተመራጭ ከማድረግ ባለፈ የገጠር ቀበሌዎች ለኑሮ የተመቹና የወደፊቱን የከተሞች ዕድገት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲለሙ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለዚህም ስኬት በዞኑ በሚገኙ 3 ወረዳዎች የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ የሚቀይሩ 24 ቤቶች መገንባታቸውንና በዕቅድ የተያዙትን ቀሪ ቤቶች ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በከተማው በመሬት ዘርፍ በሚሰጡ አገልግሎቶች የሚነሱ የማኅበረሰቡን ቅሬታዎች ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ ናቸው።


በተለይም 45 የሚጠጉ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች በመሶብ የአንድ ማዕከል እንዲሰጡ መደረጉ ለውጥ እንዳመጣም ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026

የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር ያስችላል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...

Jul 7, 2026