
አዲስ አበባ፤ ታኅሣሥ 25/2017(ኢዜአ)፦ በመንግስት በኩል ሚዲያው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁለንተናዊ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ።
ዛሬ በቅርቡ በይፋ ውህደት በፈጠሩት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት በአሁኑ መጠሪያቸው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጉብኝት አካሂደናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ያሉንን አቅሞች እየደመርን ታላቅ ሀገርን ለመገንባት ሚዲያ ትልቅ አቅም አለው ብለዋል።
ተቋሙ በዘመናዊ መሳሪያዎችና በጥራት የተደገፉ ተግባራትን የሚያከናውን መሆኑን በአካል እንደተመለከቱ ገልጸዋል።
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሁለት ጠንካራ ሚዲያ ድምር ውጤት በመሆኑ ወቅቱ የሚፈልገውን አቅምና ብቃት ተላብሶ ሀገርና ህዝብን የሚጠቅም ስራዎች መስራት እንደሚገባውም አመልክተዋል።
በዛሬ የሚዲያ ተቋሙ ምልከታችን በቀጣይ ድጋፍ የሚያሻቸው ጉዳዮች እንዳሉ ተመልክተናልም ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጣይ ዜናና ወቅታዊ፣ የምርመራና ማህበረሰብ ተኮር ስራዎችን ከተገቢ መረጃዎች ጋር ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል።
በመንግስት በኩል ሚዲያው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁለንተናዊ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026