የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በመንግስት በኩል ሚዲያው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁለንተናዊ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ታኅሣሥ 25/2017(ኢዜአ)፦ በመንግስት በኩል ሚዲያው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁለንተናዊ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ።

ዛሬ በቅርቡ በይፋ ውህደት በፈጠሩት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት በአሁኑ መጠሪያቸው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጉብኝት አካሂደናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።


ያሉንን አቅሞች እየደመርን ታላቅ ሀገርን ለመገንባት ሚዲያ ትልቅ አቅም አለው ብለዋል።

ተቋሙ በዘመናዊ መሳሪያዎችና በጥራት የተደገፉ ተግባራትን የሚያከናውን መሆኑን በአካል እንደተመለከቱ ገልጸዋል።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሁለት ጠንካራ ሚዲያ ድምር ውጤት በመሆኑ ወቅቱ የሚፈልገውን አቅምና ብቃት ተላብሶ ሀገርና ህዝብን የሚጠቅም ስራዎች መስራት እንደሚገባውም አመልክተዋል።

በዛሬ የሚዲያ ተቋሙ ምልከታችን በቀጣይ ድጋፍ የሚያሻቸው ጉዳዮች እንዳሉ ተመልክተናልም ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጣይ ዜናና ወቅታዊ፣ የምርመራና ማህበረሰብ ተኮር ስራዎችን ከተገቢ መረጃዎች ጋር ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል።

በመንግስት በኩል ሚዲያው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁለንተናዊ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026