የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ከክልሉ ከፍተኛ የመንግስት እና የፓርቲ አመራሮች ጋር በመሆን ዕድሳት የተደረገለትን የክልሉን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ጎብኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታው ወቅት እንደገለፁት የብልፅግና ፓርቲ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጪነት አዳዲስ እሳቤዎችን ተግባራዊ በማድረግ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነትን ያገኙ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል።

በተለይ ከግቢ እስከ አገር በሚል እሳቤ ፅዳትን፤ውበትን እና ምቾትን መሰረት ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን ለዜጎች፤ቱሪስቶች እና ሰራተኞች ምቹ የመኖሪያ እና የስራ አካባቢዎችን ለመፍጠር እየተሰራ ነው ብለዋል።

ይህንን መነሻ በማድረግም በክልሉ በሚከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የሐረር ከተማን የማስዋብ፤ንፁህ እና ምቹ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

ዕድሳት የተደረገለት የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ፕሮጀክትም የዚሁ ማሳያ መሆኑን ነው የገለጹት።

ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት ጎን ለጎን ተቋማቸውን ለተገልጋይ የተመቹ ውብ እና ፅዱ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በተለይም ተቋማት መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ የተገልጋይ ማረፊያዎች ማሟላት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በበኩላቸው ፓርቲው ተቋማትን ፅዱ፤ውብ እና ምቹ በማድረግ ያመጣውን ልምድ በመተግበር ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ዕድሳት የተደረገለት የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ህንፃም ይህንን መነሻ አድርጎ መከናወኑንና መሰል ተግባራትን በዘላቂነት ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

በቀጣይም ፅህፈት ቤቱን በአስፈላጊው የሰው ኃይል እና ግብዓት በማደራጀት የተቋቋመለትን አላማ እና ግብ እንዲያሳካ በትኩረት ይሰራል ማለታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

አቶ ጌቱ ለፅህፈት ቤቱ ህንፃ ዕድሳት ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ፣የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም ፣ የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ አፈ ጉባኤ አቶ ሙህየዲን አህመድ ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሮዛ ኡመርን ጨምሮ የክልሉ የመንግስትና የፓርቲ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026