
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጋትሉዋክ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በተያዘው በጀት ዓመት የጋምቤላ ከተማን ጨምሮ በክልሉ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቷል፡፡
ባለፉት ዓመታት ህብረተሰቡን በማህበራዊና በኢኮኖሚ የልማት መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የተጀመሩ በርካታ ፕሮጀክቶች ቢኖሩም በተለያዩ ምክንያቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ሳይበቁ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ በተያዘው በጀት ዓመት እነዚህን ያደሩ ፕሮጀክቶች አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የክልሉ መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በተለይም በክልሉ እየተሰሩ ያሉ የውሃ߹ የመስኖ߹ የትምህርት߹ የቢሮ ግንባታና ሌሎች ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ በጥናት ላይ ተመስርቶ ወደ ስራ መገባቱን አብራርተዋል፡፡
በጋምቤላ ከተማ ለቢሮ አገልግሎት እንዲውሉ ታስበው እየተገነቡ ያሉ ህንጻዎችን አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግም ያልተቆጠበ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የተጀመሩ ነባር ፕሮጀክቶች ሳይጠናቀቁ ከኮሪደር ልማት በስተቀር ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንደማይጀመሩም ተናግረዋል፡፡
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም በክልሉ የኮሪደር ልማት የመጀመሪያው ምዕራፍ በጋምቤላ ከተማ በይፋ መጀመሩን ጠቅሰው፤ በዞኖችና በወረዳዎችም ስራውን ለማስጀመር የግንዛቤ ማስጨበጫ መከናወኑንና በቅርቡም ወደ ትግበራ ምዕራፍ እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡
በክልሉ በመከናወን ላይ ያሉ ነባር ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ሲበቁ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ እንደሚሆኑም ገልጸዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026