የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጋትሉዋክ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በተያዘው በጀት ዓመት የጋምቤላ ከተማን ጨምሮ በክልሉ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

ባለፉት ዓመታት ህብረተሰቡን በማህበራዊና በኢኮኖሚ የልማት መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የተጀመሩ በርካታ ፕሮጀክቶች ቢኖሩም በተለያዩ ምክንያቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ሳይበቁ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡

ይሁን እንጂ በተያዘው በጀት ዓመት እነዚህን ያደሩ ፕሮጀክቶች አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የክልሉ መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡


በተለይም በክልሉ እየተሰሩ ያሉ የውሃ߹ የመስኖ߹ የትምህርት߹ የቢሮ ግንባታና ሌሎች ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ በጥናት ላይ ተመስርቶ ወደ ስራ መገባቱን አብራርተዋል፡፡

በጋምቤላ ከተማ ለቢሮ አገልግሎት እንዲውሉ ታስበው እየተገነቡ ያሉ ህንጻዎችን አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግም ያልተቆጠበ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡


በክልሉ የተጀመሩ ነባር ፕሮጀክቶች ሳይጠናቀቁ ከኮሪደር ልማት በስተቀር ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንደማይጀመሩም ተናግረዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም በክልሉ የኮሪደር ልማት የመጀመሪያው ምዕራፍ በጋምቤላ ከተማ በይፋ መጀመሩን ጠቅሰው፤ በዞኖችና በወረዳዎችም ስራውን ለማስጀመር የግንዛቤ ማስጨበጫ መከናወኑንና በቅርቡም ወደ ትግበራ ምዕራፍ እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡

በክልሉ በመከናወን ላይ ያሉ ነባር ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ሲበቁ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ እንደሚሆኑም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026