የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የክልሉ የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡


በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአሞገራ- አስጠር የ21 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ድልድዮች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል፡፡


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሐመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ለማስፋፋት እየተሰራ ነው፡፡


በክልሉ መንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን የማከናወን ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው ተናግረዋል።


ለአገልግሎት የሚበቁ ፕሮጀክቶች ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡


የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፥ በዞኑ በበጀት ዓመቱ ማህበረሰቡን በማሳተፍ በ2016 በጀት ዓመት 243 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የመንገድ ግንባታ ማከናወን ተችሏል ብለዋል።


በዚህ በጀት ዓመት ደግሞ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ210 ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ 300 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ቀበሌን ከቀበሌ እንዲሁም ወረዳን ከወረዳ የሚያገናኝ የጠጠር መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።


በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ትዛዙ ቢረዳ እንደገለፁት፥ በክልሉ ግንባታቸው የዘገየና አዲስ የተጀመሩ 830 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው እየተከናወነ ይገኛል፡፡


እነዚህን መንገዶች ደረጃ በደረጃ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።


ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የአሞገራ-አስጠር የ21 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ሌሎች አራት ድልድዮች የአካበቢው ማህበረሰብ ምርቶቻቸውን ወደ ገበያ በማውጣት ተገቢ ዋጋ እንዲያገኙ የላቀ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።


የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹን ለማጠናቀቅ ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ ማህበረሰቡ በጥንቃቄ ሊጠቀምባቸው እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡


ከመንገዱ ተጠቃሚዎች መካከል አርሶ አደር ሚስባህ መሀመድ እና አቶ መብራቴ ተክሌ በአካባቢው በመንገድ እጦት ሳቢያ ለከፍተኛ እንግልት ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።


የሚያመርቱት ምርት ሳይባክን ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአፈር ማዳበሪያ እስከ ማሳቸው ለማስገባት መንገዱ ሚናው ጉልህ ነው ብለዋል።


ሌላኛዋ የዞኑ ነዋሪ ወይዘሮ አለም አብድራህማን መንገድ እና ድልድይ ባለመኖሩ ለተለያዩ ችግሮች ሲጋለጡ መቆየታቸውን አንስተዋል።


የመንገድ እና ድልድዮቹ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት በመብቃታቸው መደሰታቸውን ገልፀው፥ ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ በጥንቃቄ ለመጠበቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025