የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የክልሉ የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡


በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአሞገራ- አስጠር የ21 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ድልድዮች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል፡፡


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሐመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ለማስፋፋት እየተሰራ ነው፡፡


በክልሉ መንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን የማከናወን ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው ተናግረዋል።


ለአገልግሎት የሚበቁ ፕሮጀክቶች ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡


የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፥ በዞኑ በበጀት ዓመቱ ማህበረሰቡን በማሳተፍ በ2016 በጀት ዓመት 243 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የመንገድ ግንባታ ማከናወን ተችሏል ብለዋል።


በዚህ በጀት ዓመት ደግሞ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ210 ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ 300 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ቀበሌን ከቀበሌ እንዲሁም ወረዳን ከወረዳ የሚያገናኝ የጠጠር መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።


በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን የጉብሬ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ትዛዙ ቢረዳ እንደገለፁት፥ በክልሉ ግንባታቸው የዘገየና አዲስ የተጀመሩ 830 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው እየተከናወነ ይገኛል፡፡


እነዚህን መንገዶች ደረጃ በደረጃ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።


ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የአሞገራ-አስጠር የ21 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ሌሎች አራት ድልድዮች የአካበቢው ማህበረሰብ ምርቶቻቸውን ወደ ገበያ በማውጣት ተገቢ ዋጋ እንዲያገኙ የላቀ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።


የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹን ለማጠናቀቅ ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ ማህበረሰቡ በጥንቃቄ ሊጠቀምባቸው እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡


ከመንገዱ ተጠቃሚዎች መካከል አርሶ አደር ሚስባህ መሀመድ እና አቶ መብራቴ ተክሌ በአካባቢው በመንገድ እጦት ሳቢያ ለከፍተኛ እንግልት ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።


የሚያመርቱት ምርት ሳይባክን ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአፈር ማዳበሪያ እስከ ማሳቸው ለማስገባት መንገዱ ሚናው ጉልህ ነው ብለዋል።


ሌላኛዋ የዞኑ ነዋሪ ወይዘሮ አለም አብድራህማን መንገድ እና ድልድይ ባለመኖሩ ለተለያዩ ችግሮች ሲጋለጡ መቆየታቸውን አንስተዋል።


የመንገድ እና ድልድዮቹ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት በመብቃታቸው መደሰታቸውን ገልፀው፥ ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ በጥንቃቄ ለመጠበቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026