በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ የሚታይ ምንነቱ ያልታወቀ ተቀጣጣይ ነገር መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች በተለያዩ አማራጮች መረጃውን አጋርተዋል።
ተቀጣጣይ ነገሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፎቶ እና በተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ለመመልከት ተችሏል።
ጉዳዩ የብዙዎችንም ቀልብ የሳበ ጉዳይ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ስፔን ሳይንስ ሶሳይቲ ትናንት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸውን አስመልክቶ ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።
ሶሳይቲው በደረሰው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ባደረገው ምልክታ የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ ሲል አመልክቷል።
ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ነው ያስታወቀው።
የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት እንዲቻል ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ገልጿል።
ይህ የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ ሶሳይቲው አሳስቧል።
በተጨማሪም ሶሳይቲው የቁስ አካላቱን አስመልክቶ እያደረገ ላለው ማጣራት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ የቀረጿቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎች በመላክ ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025