
በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ የሚታይ ምንነቱ ያልታወቀ ተቀጣጣይ ነገር መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች በተለያዩ አማራጮች መረጃውን አጋርተዋል።
ተቀጣጣይ ነገሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፎቶ እና በተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ለመመልከት ተችሏል።
ጉዳዩ የብዙዎችንም ቀልብ የሳበ ጉዳይ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ስፔን ሳይንስ ሶሳይቲ ትናንት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸውን አስመልክቶ ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።
ሶሳይቲው በደረሰው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ባደረገው ምልክታ የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ ሲል አመልክቷል።
ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ነው ያስታወቀው።
የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት እንዲቻል ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ገልጿል።
ይህ የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ ሶሳይቲው አሳስቧል።
በተጨማሪም ሶሳይቲው የቁስ አካላቱን አስመልክቶ እያደረገ ላለው ማጣራት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ የቀረጿቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎች በመላክ ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026