የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍሎች ትናንት ስለታዩት የቁስ አካላት እስከ አሁን የምናውቃቸው ጉዳዮች

Jan 13, 2025

IDOPRESS

በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ የሚታይ ምንነቱ ያልታወቀ ተቀጣጣይ ነገር መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች በተለያዩ አማራጮች መረጃውን አጋርተዋል።

ተቀጣጣይ ነገሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፎቶ እና በተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ለመመልከት ተችሏል።

ጉዳዩ የብዙዎችንም ቀልብ የሳበ ጉዳይ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ስፔን ሳይንስ ሶሳይቲ ትናንት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸውን አስመልክቶ ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።

ሶሳይቲው በደረሰው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ባደረገው ምልክታ የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ ሲል አመልክቷል።

ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ነው ያስታወቀው።

የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት እንዲቻል ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ገልጿል።

ይህ የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ ሶሳይቲው አሳስቧል።

በተጨማሪም ሶሳይቲው የቁስ አካላቱን አስመልክቶ እያደረገ ላለው ማጣራት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ የቀረጿቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎች በመላክ ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026