
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2017(ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (ESX) መርቀው መክፈታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ይኽ ተግባር የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ በማዘመን ረገድ ዐቢይ ርምጃ መሆኑንም ገልጿል።
ESX ለዘርፉ ግልፅነትን የተላበሰ የገበያ ስፍራ ይፈጥራል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል።

በሁለተኛው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ጥላ ሥርም በኢንቨስትመንት ለሚመራ እድገት በር ይከፍታል ነው ያለው።
በመንግሥትም በግልም ዘርፎች የፋይናንስ አካታችነትን በማስፋት የቁጠባ እንቅስቃሴን ማሳደግን ብሎም ኢንቨስተሮችን መጠበቅን ታላሚ አድርጎ ተነስቷል ሲልም ገልጿል።
ESX በሶስት የገበያ ክፍሎች ላይ ይሰራል ያለው ጽህፈት ቤቱ እነዚህም ለቢዝነስ ተቋማት፣ ለመንግሥት እና ሌሎች ተቋማት የሚያገለግሉ የይዞታ ገበያ፣ የቋሚ ገቢ ገበያ እና የገንዘብ ገበያ ናቸው ብሏል።

የሙከራ የገንዘብ ገበያው ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ እንቅስቃሴ ተካሂዶበታል ሲልም አስታውቋል።
ይኽም ገበያው የኢትዮጵያን የፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር ብሎም ለዘላቂ ልማት የካፒታል አቅም ለማሰባሰብ ያለውን አቅም አሳይቷል ነው ያለው።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026