ባሕር ዳር፤ ጥር 05/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ሕገ ወጥ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለጸ።
ቢሮው የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት እንዲቻል ከተለያዩ የሀብት ምንጭች በማሰባሰብ 960 ሚሊዮን ብር መመደቡን አስታውቋል።
የቢሮው ሃላፊ ኢብራሒም ሙሐመድ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ የክልሉን ሰላም ከማጽናት በተጓዳኝ የገበያ ዋጋን የማረጋጋት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
በተለይም ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ህገ ወጥ ግብይት ላይ ተሰማርተው በተገኙ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።
በግማሽ ዓመቱ በሕገ-ወጥ ግብይት የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ከ55 ሺህ 454 በላይ ነጋዴዎች በሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጽሙ መያዙን ገልጸዋል።
በዚህም እንደ ጥፋታቸው ከማስጠቀቂያ እሰከ ማገድ እንዲሁም በሕግ ተጠያቂ እስከ ማድረግ የደረሱ እርምጃዎች ተወስደዋል ነው ያሉት።
ነጋዴዎቹ ያለንግድ ፈቃድ ግብይት በመፈጸም፣ በምርት ጥራት ጉድለት፣ ትክክለኛ ያልሆነ የመለኪያ መሳሪያ በመጠቀም፣ በተጋነነ ዋጋ እና ያለደረሰኝ በመሸጥ ተጠርጥረው የተያዙ ናቸው ብለዋል።
ከ250 ሺህ ሊትር ነዳጅና አምስት ሺህ 573 ኩንታል የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች መያዙንም እንዲሁ።
ከሕገ ወጥ ግብይት ቁጥጥር ባሻገር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች ሀብት የማሰባሰብና የብድር አማራጭ በማቅረብ፣ የሕብረት ስራ ማህበራትን የካፒታል አቅም ችግር በመፍታትም ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ለአብነትም 960 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች በማመቻቸት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው በማቅረብ ለገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡ ሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጸም ሲያስተውል ለሚመለከተው አካል ፈጣን ጥቆማ በመስጠት ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025