የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በአማራ ክልል ገበያ አለመረጋጋት በሚዳርግ ሕገ ወጥ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው- ቢሮው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ ጥር 05/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ሕገ ወጥ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለጸ።

ቢሮው የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት እንዲቻል ከተለያዩ የሀብት ምንጭች በማሰባሰብ 960 ሚሊዮን ብር መመደቡን አስታውቋል።

የቢሮው ሃላፊ ኢብራሒም ሙሐመድ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ የክልሉን ሰላም ከማጽናት በተጓዳኝ የገበያ ዋጋን የማረጋጋት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

በተለይም ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ህገ ወጥ ግብይት ላይ ተሰማርተው በተገኙ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።

በግማሽ ዓመቱ በሕገ-ወጥ ግብይት የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ከ55 ሺህ 454 በላይ ነጋዴዎች በሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጽሙ መያዙን ገልጸዋል።

በዚህም እንደ ጥፋታቸው ከማስጠቀቂያ እሰከ ማገድ እንዲሁም በሕግ ተጠያቂ እስከ ማድረግ የደረሱ እርምጃዎች ተወስደዋል ነው ያሉት።

ነጋዴዎቹ ያለንግድ ፈቃድ ግብይት በመፈጸም፣ በምርት ጥራት ጉድለት፣ ትክክለኛ ያልሆነ የመለኪያ መሳሪያ በመጠቀም፣ በተጋነነ ዋጋ እና ያለደረሰኝ በመሸጥ ተጠርጥረው የተያዙ ናቸው ብለዋል።

ከ250 ሺህ ሊትር ነዳጅና አምስት ሺህ 573 ኩንታል የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች መያዙንም እንዲሁ።

ከሕገ ወጥ ግብይት ቁጥጥር ባሻገር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች ሀብት የማሰባሰብና የብድር አማራጭ በማቅረብ፣ የሕብረት ስራ ማህበራትን የካፒታል አቅም ችግር በመፍታትም ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለአብነትም 960 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች በማመቻቸት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው በማቅረብ ለገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

ህብረተሰቡ ሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጸም ሲያስተውል ለሚመለከተው አካል ፈጣን ጥቆማ በመስጠት ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026