የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በአማራ ክልል ገበያ አለመረጋጋት በሚዳርግ ሕገ ወጥ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው- ቢሮው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ ጥር 05/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ሕገ ወጥ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለጸ።

ቢሮው የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት እንዲቻል ከተለያዩ የሀብት ምንጭች በማሰባሰብ 960 ሚሊዮን ብር መመደቡን አስታውቋል።

የቢሮው ሃላፊ ኢብራሒም ሙሐመድ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ የክልሉን ሰላም ከማጽናት በተጓዳኝ የገበያ ዋጋን የማረጋጋት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

በተለይም ለገበያ አለመረጋጋት በሚዳርጉ ህገ ወጥ ግብይት ላይ ተሰማርተው በተገኙ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።

በግማሽ ዓመቱ በሕገ-ወጥ ግብይት የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ከ55 ሺህ 454 በላይ ነጋዴዎች በሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጽሙ መያዙን ገልጸዋል።

በዚህም እንደ ጥፋታቸው ከማስጠቀቂያ እሰከ ማገድ እንዲሁም በሕግ ተጠያቂ እስከ ማድረግ የደረሱ እርምጃዎች ተወስደዋል ነው ያሉት።

ነጋዴዎቹ ያለንግድ ፈቃድ ግብይት በመፈጸም፣ በምርት ጥራት ጉድለት፣ ትክክለኛ ያልሆነ የመለኪያ መሳሪያ በመጠቀም፣ በተጋነነ ዋጋ እና ያለደረሰኝ በመሸጥ ተጠርጥረው የተያዙ ናቸው ብለዋል።

ከ250 ሺህ ሊትር ነዳጅና አምስት ሺህ 573 ኩንታል የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች መያዙንም እንዲሁ።

ከሕገ ወጥ ግብይት ቁጥጥር ባሻገር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች ሀብት የማሰባሰብና የብድር አማራጭ በማቅረብ፣ የሕብረት ስራ ማህበራትን የካፒታል አቅም ችግር በመፍታትም ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለአብነትም 960 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የሀብት ምንጮች በማመቻቸት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው በማቅረብ ለገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

ህብረተሰቡ ሕገ-ወጥ ግብይት ሲፈጸም ሲያስተውል ለሚመለከተው አካል ፈጣን ጥቆማ በመስጠት ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026