አዲስ አበባ፤ ጥር 5 /2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ።
ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የአፍሪካ ቀንድ እና የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኢስሃኩ ማቱምቢ ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትሯ በኢትዮጵያና በቀጣናው አገራት የተከናወኑ ስራዎችና በመልካም ተሞክሮ መቀመር አስፈላጊነት ላይ ውይይት መደረጉን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
የዩኤን ሃቢታት ቀጣይ ስትራቴጂካዊ ትኩረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞችና አገራዊ የልማት ስትራቴጂክ ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን እንደሚሰራ አመልክተዋል።
በቀጣይም ሁለቱ ወገኖች በሀገራዊ፤ ቀጣናዊና አህጉራዊ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በቀጣይ መጋቢት ወር ለዩኤን ሀቢታት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለምታቀርበው የመልካም ተሞክሮና የከተማ ልማት የመሪነት ሚና ዝግጅት መጀመሯን ለዳይሬክተሩ መግለጻቸውን ነው ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025