
አዲስ አበባ፤ ጥር 5 /2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ።
ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የአፍሪካ ቀንድ እና የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኢስሃኩ ማቱምቢ ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትሯ በኢትዮጵያና በቀጣናው አገራት የተከናወኑ ስራዎችና በመልካም ተሞክሮ መቀመር አስፈላጊነት ላይ ውይይት መደረጉን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
የዩኤን ሃቢታት ቀጣይ ስትራቴጂካዊ ትኩረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞችና አገራዊ የልማት ስትራቴጂክ ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን እንደሚሰራ አመልክተዋል።
በቀጣይም ሁለቱ ወገኖች በሀገራዊ፤ ቀጣናዊና አህጉራዊ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በቀጣይ መጋቢት ወር ለዩኤን ሀቢታት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለምታቀርበው የመልካም ተሞክሮና የከተማ ልማት የመሪነት ሚና ዝግጅት መጀመሯን ለዳይሬክተሩ መግለጻቸውን ነው ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026