የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር ማጠናከር ትሻለች- ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 5 /2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የአፍሪካ ቀንድ እና የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኢስሃኩ ማቱምቢ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትሯ በኢትዮጵያና በቀጣናው አገራት የተከናወኑ ስራዎችና በመልካም ተሞክሮ መቀመር አስፈላጊነት ላይ ውይይት መደረጉን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

የዩኤን ሃቢታት ቀጣይ ስትራቴጂካዊ ትኩረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞችና አገራዊ የልማት ስትራቴጂክ ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በቀጣይም ሁለቱ ወገኖች በሀገራዊ፤ ቀጣናዊና አህጉራዊ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በቀጣይ መጋቢት ወር ለዩኤን ሀቢታት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለምታቀርበው የመልካም ተሞክሮና የከተማ ልማት የመሪነት ሚና ዝግጅት መጀመሯን ለዳይሬክተሩ መግለጻቸውን ነው ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025