የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር ማጠናከር ትሻለች- ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 5 /2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዩኤን ሀቢታት ጋር ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የአፍሪካ ቀንድ እና የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኢስሃኩ ማቱምቢ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትሯ በኢትዮጵያና በቀጣናው አገራት የተከናወኑ ስራዎችና በመልካም ተሞክሮ መቀመር አስፈላጊነት ላይ ውይይት መደረጉን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

የዩኤን ሃቢታት ቀጣይ ስትራቴጂካዊ ትኩረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞችና አገራዊ የልማት ስትራቴጂክ ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በቀጣይም ሁለቱ ወገኖች በሀገራዊ፤ ቀጣናዊና አህጉራዊ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በቀጣይ መጋቢት ወር ለዩኤን ሀቢታት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለምታቀርበው የመልካም ተሞክሮና የከተማ ልማት የመሪነት ሚና ዝግጅት መጀመሯን ለዳይሬክተሩ መግለጻቸውን ነው ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026