የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አክሱም፣ጥር 6/2017 (ኢዜአ)፦በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ።

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሐዱሽ ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ የአክሱም ተለዋጭ መናኸሪያን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች እየተካሄዱ ነው።

የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው ብለዋል።

ከሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የ1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣የመንገድ ዳር መብራትና የ5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።

በተጨማሪም በክረምት ወራት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች 1 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጎርፍ መውረጃ ቦይ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል።

የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹም ለ1 ሺህ 400 ስራ አጥ ወገኖች የስራ እድል ተፈጥሯል።

የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል የንግስተ ሳባ ቀበሌ ነዋሪው ወጣት አቤሰሎም ዜናዊ ከሥራው በሚያገኘው ገቢ የመነሻ ካፒታል ተጠቅሞ የግሉን ስራ ለመጀመር ሀሳብ እንዳለው ገልጿል።

የሐወልቲ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሙሉ ካህሳይ በበኩሏ በተፈጠረላት የስራ ዕድል በምታገኘው ገቢ ወደ ዘላቂ ሥራ ለመሸጋገር እቅድ እንዳላት ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026