አክሱም፣ጥር 6/2017 (ኢዜአ)፦በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሐዱሽ ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ የአክሱም ተለዋጭ መናኸሪያን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች እየተካሄዱ ነው።
የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው ብለዋል።
ከሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የ1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣የመንገድ ዳር መብራትና የ5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።
በተጨማሪም በክረምት ወራት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች 1 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጎርፍ መውረጃ ቦይ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል።
የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹም ለ1 ሺህ 400 ስራ አጥ ወገኖች የስራ እድል ተፈጥሯል።
የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል የንግስተ ሳባ ቀበሌ ነዋሪው ወጣት አቤሰሎም ዜናዊ ከሥራው በሚያገኘው ገቢ የመነሻ ካፒታል ተጠቅሞ የግሉን ስራ ለመጀመር ሀሳብ እንዳለው ገልጿል።
የሐወልቲ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሙሉ ካህሳይ በበኩሏ በተፈጠረላት የስራ ዕድል በምታገኘው ገቢ ወደ ዘላቂ ሥራ ለመሸጋገር እቅድ እንዳላት ተናግራለች።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025