
አክሱም፣ጥር 6/2017 (ኢዜአ)፦በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሐዱሽ ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ የአክሱም ተለዋጭ መናኸሪያን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች እየተካሄዱ ነው።
የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው ብለዋል።
ከሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የ1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣የመንገድ ዳር መብራትና የ5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።
በተጨማሪም በክረምት ወራት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች 1 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጎርፍ መውረጃ ቦይ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል።
የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹም ለ1 ሺህ 400 ስራ አጥ ወገኖች የስራ እድል ተፈጥሯል።
የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል የንግስተ ሳባ ቀበሌ ነዋሪው ወጣት አቤሰሎም ዜናዊ ከሥራው በሚያገኘው ገቢ የመነሻ ካፒታል ተጠቅሞ የግሉን ስራ ለመጀመር ሀሳብ እንዳለው ገልጿል።
የሐወልቲ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሙሉ ካህሳይ በበኩሏ በተፈጠረላት የስራ ዕድል በምታገኘው ገቢ ወደ ዘላቂ ሥራ ለመሸጋገር እቅድ እንዳላት ተናግራለች።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026