የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በምንከፍለው ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡነበት መሆኑን በመገንዘባችን ግብራችንን በወቅቱ ከፍለናል - ግብር ከፋዮች</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

ሠመራ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በምንከፍለው ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡ መሆናቸውን በመገንዘባችን ግብራችንን በወቅቱ ከፍለናል ሲሉ የአፋር ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ።

በክልሉ የሠመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ግብር ከፋይ አቶ አንዋር መኮንን እንዳሉት እኛ የምንከፍለው ግብር መልሶ ለህዝብ ጥቅም የሚውሉ ልማቶች በጊዜያቸው እንዲጠናቀቁ ያደርጋል።

በዚሁ ግንዛቤ ግብራቸውን በጊዜው በመክፈላቸው የተለያዩ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ ከማድረግ ባለፈ ለሀገር እድገት የራሳቸውን ሃላፊነት በወቅቱ እንዲወጡ እንዳስቻላቸውም ተናግረዋል።

ግብር በመክፈላቸው መንገዶች፣ ጤና ተቋማት እና ትምህርት ቤቶች እንዲገነቡ ዕድል የሚሰጥ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላው ግብር ከፋይ አቶ አወል ኢድሪስ ናቸው።

በመሆኑም ሁሉም ሰው የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ እንዲከፍል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሠብሰቡን ገልጿል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ አወል አብዱ ለኢዜአ እንደገለፁት በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በግማሽ መጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ከዚህም 2 ቢሊዮን 671 ሚሊዮን 393ሺህ አራት ብር መሠብሰቡን ገልጸው፤ በዚህም የዕቅዱን 97 በመቶ ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

ይኸም ባለፈው ዓመት ተመሣሣይ ወቅት ከተሰበሰበው ጋር ሲነፃፀር ከ794 ሚሊየን ብር በላይ ብልጫ ያለውና በመቶኛም የ42 በመቶ ብልጫ የታየበት መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ሃላፊው ገለጻ፤ የተሻለ አፈጻጸም ሊኖር የቻለው በወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ላይ የግንዛቤ ማሣደጊያ ስራዎች በመከናወናቸውና ባለሙያዎችም በቁርጠኝነት በመሥራታቸው ነው።

ይህም ሆኖ ከደረሠኝ አሰጣጥና አቆራረጥ ጋር አሁንም የሚስተዋሉ ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ሃላፊነታቸውን በማይወጡ ግብር ከፋዮች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025