የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ግብ ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን ዕውን ማድረግ ነው።
ዘርፉ የኢንዱስትሪላይዜሽን ጉዞ መስፈንጠሪያ ነው። በተለይም የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀሩ ሀገራዊ ተኪ ምርቶችን በማምረት።
በዚህም ተቋማቱ አንድም በምርምርና ፈጠራ ስራዎችን ውጤታማ መሆን፣ አንድም በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁና በቂ የሰው ኃይል የማፍራት ግብ ሰንቀው ይሰራሉ።
ተቋማቱ የፈጠራ ውጤቶችን በተግባር ከማዋል በዘለለ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ረገድም አይተኬ ሚና ይጫወታሉ።
በኢትዮጵያም ይህ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶት በርካታ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ተቋቁመው ወደስራ ገብተዋል።
ለመሆኑ ተቋማቱ በችግር ፈቺ የፈጠራ ምርቶች ምን ያህል ውጤታማ ሆነዋል የሚለውን ኢዜአ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ለአብነት ቃኝቷል።
የኮሌጁ መምህር ወርቁ ፈንታሁን እና ተማሪ ዳግም ጋርጦ ኮሌጁ እና የኮሌጁ ሰልጣኞች ቁልፍ ግባቸው ችግር ፈቺነት ነው ብለው ያምናሉ።
መምህሩና ደቀ መዝሙሩም በቅርብ የተመለከቱትን ችግር የሚፈታ የፈጠራ ስራ ለማውጣት ወሰነው ወደስራ ገብተዋል።
መምህር ወርቁ ከሩቅ ሳይሆን ከቅርብ ችግር ተነስተው የእንስሳት መኖ ማቀነባበርያ ማሽን መስራት ችለዋል።
ይሄውም በሚያስተምሩበት የጀኔራል ዊንጌት ኮሌጅ የሚካሄደውን የከብት እርባታና ማድለብ ስራ ጋር ተያይዞ የተፈጠረው የመኖ እጥረት የመኖ ማቀነባበሪያ ለማምረት ምክንያት ሆኗቸዋል።
ፈጠራቸውም የኮሌጁን ችግር አቃሏል። ይኼውም ኮሌጁ ለእንስሳት መኖ ግዢ የሚያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ማስቀረታቸው ነው።
መምህር ወርቁ እንደሚሉት ማሽኑ ከውጭ ቢገባ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚጠይቅ ሲሆን እርሳቸው ግን በ400 ሺህ ብር ብቻ ሀገር ውስጥ መተካት ችለዋል።
ማሽናቸው በሰዓት 4 ኩንታል፤ በቀን ደግሞ 15 ኩንታል መኖ ያቀነባበራል። ከአዋጭነት አኳያም በወር እስከ 100 ሺህ ብር ትርፍ ያስገኛል ይላሉ።
የመኖ ማቀነባበርያ ማሽኑን በብዛት አምርቶ በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና ለተሰማሩ አካላት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ይገልጻሉ።
የኮሌጁ ተማሪ ዳግም ጋርጦ ደግሞ አካል ጉዳተኞችን፣ አቅመ ደካሞችንና ህፃናትን መመገብ የሚያስችል ሮቦት ነው የሰራው።
ሮቦቱ ለአንድ ሰው በቀን የሚመገበውን ምግብ እና የሚጠጣውን ውሃ በልኬት በተሰጠው መጠን ልክ ድጋፍ ለሚሹ ህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል።
ለህብረተሰቡ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ መስራት ለሀገር ያለውን ወሳኝ ፋይዳ የሚያነሳው ዳግም፤ ለዚህ ደግሞ ለዘርፉ ምቹ ምህዳር ሊፈጠር እንደሚገባ ያነሳል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ልጋኔ እንደሚሉት በከተማዋ በሚገኙ 15 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቁና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ተተኩሯል።
ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ እንደሆነም ይገልጻሉ።
እስካሁንም ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ጥሬ ግብዓቶች በመጠቀም ተኪ ምርቶችን በማምረት ምሳሌ የሆኑ ኮሌጆች እንዳሉ የጀኔራል ዊንጌትን ለአብነት ይጠቅሳሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025