
የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ግብ ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን ዕውን ማድረግ ነው።
ዘርፉ የኢንዱስትሪላይዜሽን ጉዞ መስፈንጠሪያ ነው። በተለይም የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀሩ ሀገራዊ ተኪ ምርቶችን በማምረት።
በዚህም ተቋማቱ አንድም በምርምርና ፈጠራ ስራዎችን ውጤታማ መሆን፣ አንድም በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁና በቂ የሰው ኃይል የማፍራት ግብ ሰንቀው ይሰራሉ።
ተቋማቱ የፈጠራ ውጤቶችን በተግባር ከማዋል በዘለለ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ረገድም አይተኬ ሚና ይጫወታሉ።
በኢትዮጵያም ይህ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶት በርካታ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ተቋቁመው ወደስራ ገብተዋል።
ለመሆኑ ተቋማቱ በችግር ፈቺ የፈጠራ ምርቶች ምን ያህል ውጤታማ ሆነዋል የሚለውን ኢዜአ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ለአብነት ቃኝቷል።
የኮሌጁ መምህር ወርቁ ፈንታሁን እና ተማሪ ዳግም ጋርጦ ኮሌጁ እና የኮሌጁ ሰልጣኞች ቁልፍ ግባቸው ችግር ፈቺነት ነው ብለው ያምናሉ።
መምህሩና ደቀ መዝሙሩም በቅርብ የተመለከቱትን ችግር የሚፈታ የፈጠራ ስራ ለማውጣት ወሰነው ወደስራ ገብተዋል።
መምህር ወርቁ ከሩቅ ሳይሆን ከቅርብ ችግር ተነስተው የእንስሳት መኖ ማቀነባበርያ ማሽን መስራት ችለዋል።
ይሄውም በሚያስተምሩበት የጀኔራል ዊንጌት ኮሌጅ የሚካሄደውን የከብት እርባታና ማድለብ ስራ ጋር ተያይዞ የተፈጠረው የመኖ እጥረት የመኖ ማቀነባበሪያ ለማምረት ምክንያት ሆኗቸዋል።
ፈጠራቸውም የኮሌጁን ችግር አቃሏል። ይኼውም ኮሌጁ ለእንስሳት መኖ ግዢ የሚያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ማስቀረታቸው ነው።
መምህር ወርቁ እንደሚሉት ማሽኑ ከውጭ ቢገባ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚጠይቅ ሲሆን እርሳቸው ግን በ400 ሺህ ብር ብቻ ሀገር ውስጥ መተካት ችለዋል።
ማሽናቸው በሰዓት 4 ኩንታል፤ በቀን ደግሞ 15 ኩንታል መኖ ያቀነባበራል። ከአዋጭነት አኳያም በወር እስከ 100 ሺህ ብር ትርፍ ያስገኛል ይላሉ።
የመኖ ማቀነባበርያ ማሽኑን በብዛት አምርቶ በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና ለተሰማሩ አካላት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ይገልጻሉ።
የኮሌጁ ተማሪ ዳግም ጋርጦ ደግሞ አካል ጉዳተኞችን፣ አቅመ ደካሞችንና ህፃናትን መመገብ የሚያስችል ሮቦት ነው የሰራው።
ሮቦቱ ለአንድ ሰው በቀን የሚመገበውን ምግብ እና የሚጠጣውን ውሃ በልኬት በተሰጠው መጠን ልክ ድጋፍ ለሚሹ ህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል።
ለህብረተሰቡ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ መስራት ለሀገር ያለውን ወሳኝ ፋይዳ የሚያነሳው ዳግም፤ ለዚህ ደግሞ ለዘርፉ ምቹ ምህዳር ሊፈጠር እንደሚገባ ያነሳል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ልጋኔ እንደሚሉት በከተማዋ በሚገኙ 15 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቁና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ተተኩሯል።
ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ እንደሆነም ይገልጻሉ።
እስካሁንም ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ጥሬ ግብዓቶች በመጠቀም ተኪ ምርቶችን በማምረት ምሳሌ የሆኑ ኮሌጆች እንዳሉ የጀኔራል ዊንጌትን ለአብነት ይጠቅሳሉ።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026