የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ለመፍጠር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ።

የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፥ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሐመድ ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ የዘላቂ ልማት ግቦች ትግበራን ማፋጠን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።

ኢትዮጵያ እየተገበረች የምትገኘው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሞች፣ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ጉባዔ አስመልክቶ እያደረገች ያለው ዝግጅት ሌሎች የውይይት አጀንዳዎች ናቸው።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቡድን (UNCT) እና የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ያላቸውን አጋርነት በማጠናከር የኢትዮጵያን የልማት አጀንዳ መደገፍ የሚያስችል ግልጽ የኃላፊነት ተዋረድ መዘርጋት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል።


የገንዘብ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የልማት ግቦቹን አፈጻጸም ለማሻሻል የቀየሰቻቸውን ስትራቴጂዎች አስመልክቶ ለምክትል ዋና ፀሐፊዋ ገለጻ አድርገዋል።

ሚኒስትሩ ለግቦቹ መሳካት ጠንካራ ትብብር እና ለትግበራው የሚያስፈልገውን የፋይናንስ መጠን ማሳደግ እንደሚገባ አንስተዋል።

የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የልማት ግቦች እንዲሳኩ እያደረጉት ላለው ጥረት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።

ሁለቱ ወገኖች የኢትዮጵያ መንግስት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተለያዩ ተቋማት እና አደረጃጀቶች የዘላቂ ልማት ግቦችን እንደ ሀገር ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ጋር አጣጥሞ ማስኬድ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከተመድ ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር እና በዓለም መድረክ የአፍሪካ ልማት ግቦች እንዲሳኩ የበኩሏን ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትሩ የገለጹት።

ኢትዮጵያ እና ተመድ የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ በውይይቱ ወቅት መገለጹን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025