የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የጥምቀት በዓል ከኃይማኖታዊ እሴቱ ባሻገር የከተማችንን መልካም ገጽታ የሚያስተዋውቅ ነው- የባቱ ከተማ ነዋሪዎች</p>

Jan 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፦የጥምቀትበዓልከኃይማኖታዊእሴቱባሻገርየከተማዋንመልካምገጽታበማስተዋወቅየኢኮኖሚተጠቃሚነታቸውንእያረጋገጠላቸውመሆኑንየባቱከተማነዋሪዎችገለጹ፡፡


በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ የሚከበረውን የጥምቀት በዓል ለመታደም ወደ አካባቢው የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው አስፈላጊውን ሁሉ ማዘጋጀታቸውን በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ገልጸዋል፡፡

የጥምቀት በዓል ከኃይማኖታዊ እሴቶች ባሻገር በርካታ ማህበራዊና ባህላዊ ትውፊቶች የሚንጸባረቁበት ነው።


በባቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓልም በርካታ ቱሪስቶች የሚሳተፉበት መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል።

ባቱና አካባቢው የቱሪስት ኮሪደር መሆኑን ተከትሎ የአካባቢውን የተፈጥሮ፣ የባህልና የቱሪስት መስህብ የበለጠ በማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርም ነው፡፡


በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ በማህበር ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ ወጣቶች በጥምቀት በዓል አከባቢያቸውን በማስተዋወቅ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በኃይቁ በሞተር ጀልባ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሳቃሳ በሪሶ በጥምቀት በዓል ለቱሪስቶች የጀልባ አገልግሎት በመስጠት አከባቢያቸውን እያስተዋወቁ ገቢም ለማግኘት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡


ለእንግዶች የተሟላ የጀልባ አገልግሎት በመስጠት ላይ እነደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡

በኃይቁ አካባቢ የዓሳ ምርቶችን በማቅረብ የሚተዳደሩት ወጣት ዙሪያሽ ግርማና አማኑኤል ወልደጊዮርጊስ፤ የጥምቀት በዓልን ለመታደም ወደ ከተማዋ የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በኃይቁ ዳርቻዎች የዓሳ ምርቶችን ለቱሪዝቶች ለማቅረብ መዘጋጀታቸውንም ነው የጠቆሙት፡፡

ከምስራቅ ሀረርጌ በዓሉ ላይ ለመታደም የመጡት አቶ ሸዋንግዛው ንጉሴ በአካባቢው በተደረገላቸው መልካም አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።

በኃይቁ ዳርቻ አካባቢዎች ያለውን ውብ መልካዐ ምድር ለማልማት የተደረገው ጥረትም እጅግ የሚያስደስት ነው ብለዋል፡፡

በአካባቢው የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ይበልጥ በማስፋፋት በርካታ ጎብኚዎችን ወደ ለመሳብ መሰራት እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡

ወይዘሮ ጫልቱ ቃበቶ በበኩላቸው ኃይቁን ለቱሪዝም ገቢ ለማዋል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026