
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፦የጥምቀትበዓልከኃይማኖታዊእሴቱባሻገርየከተማዋንመልካምገጽታበማስተዋወቅየኢኮኖሚተጠቃሚነታቸውንእያረጋገጠላቸውመሆኑንየባቱከተማነዋሪዎችገለጹ፡፡

በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ የሚከበረውን የጥምቀት በዓል ለመታደም ወደ አካባቢው የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው አስፈላጊውን ሁሉ ማዘጋጀታቸውን በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ገልጸዋል፡፡
የጥምቀት በዓል ከኃይማኖታዊ እሴቶች ባሻገር በርካታ ማህበራዊና ባህላዊ ትውፊቶች የሚንጸባረቁበት ነው።

በባቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓልም በርካታ ቱሪስቶች የሚሳተፉበት መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል።
ባቱና አካባቢው የቱሪስት ኮሪደር መሆኑን ተከትሎ የአካባቢውን የተፈጥሮ፣ የባህልና የቱሪስት መስህብ የበለጠ በማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርም ነው፡፡

በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ በማህበር ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ ወጣቶች በጥምቀት በዓል አከባቢያቸውን በማስተዋወቅ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በኃይቁ በሞተር ጀልባ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሳቃሳ በሪሶ በጥምቀት በዓል ለቱሪስቶች የጀልባ አገልግሎት በመስጠት አከባቢያቸውን እያስተዋወቁ ገቢም ለማግኘት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡

ለእንግዶች የተሟላ የጀልባ አገልግሎት በመስጠት ላይ እነደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
በኃይቁ አካባቢ የዓሳ ምርቶችን በማቅረብ የሚተዳደሩት ወጣት ዙሪያሽ ግርማና አማኑኤል ወልደጊዮርጊስ፤ የጥምቀት በዓልን ለመታደም ወደ ከተማዋ የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በኃይቁ ዳርቻዎች የዓሳ ምርቶችን ለቱሪዝቶች ለማቅረብ መዘጋጀታቸውንም ነው የጠቆሙት፡፡
ከምስራቅ ሀረርጌ በዓሉ ላይ ለመታደም የመጡት አቶ ሸዋንግዛው ንጉሴ በአካባቢው በተደረገላቸው መልካም አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።
በኃይቁ ዳርቻ አካባቢዎች ያለውን ውብ መልካዐ ምድር ለማልማት የተደረገው ጥረትም እጅግ የሚያስደስት ነው ብለዋል፡፡
በአካባቢው የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ይበልጥ በማስፋፋት በርካታ ጎብኚዎችን ወደ ለመሳብ መሰራት እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡
ወይዘሮ ጫልቱ ቃበቶ በበኩላቸው ኃይቁን ለቱሪዝም ገቢ ለማዋል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026