አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን የሚውል 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸው ተገለጸ።
የምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
እስከ አሁን 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውንና ከዚህ ጭነት ውስጥ 256 ሺህ 398 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ገልጿል።
ቀሪው ማዳበሪያ በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኝም ነው የጠቆመው።
በተጨማሪም 56 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች ሰባተኛ መርከብ ትናንት ዶራሌ ሁለገብ ወደብ ደርሳ ጭነት በማራገፍ ላይ መሆኗንም አመልክቷል።
በሚቀጥሉት ቀናትም ተጨማሪ አራት አፈር ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጂቡቲ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025