
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን የሚውል 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸው ተገለጸ።
የምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
እስከ አሁን 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውንና ከዚህ ጭነት ውስጥ 256 ሺህ 398 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ገልጿል።
ቀሪው ማዳበሪያ በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኝም ነው የጠቆመው።

በተጨማሪም 56 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች ሰባተኛ መርከብ ትናንት ዶራሌ ሁለገብ ወደብ ደርሳ ጭነት በማራገፍ ላይ መሆኗንም አመልክቷል።
በሚቀጥሉት ቀናትም ተጨማሪ አራት አፈር ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጂቡቲ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቋል።

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026