
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን የሚውል 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸው ተገለጸ።
የምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
እስከ አሁን 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውንና ከዚህ ጭነት ውስጥ 256 ሺህ 398 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ገልጿል።
ቀሪው ማዳበሪያ በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኝም ነው የጠቆመው።

በተጨማሪም 56 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች ሰባተኛ መርከብ ትናንት ዶራሌ ሁለገብ ወደብ ደርሳ ጭነት በማራገፍ ላይ መሆኗንም አመልክቷል።
በሚቀጥሉት ቀናትም ተጨማሪ አራት አፈር ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጂቡቲ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቋል።

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026