
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን የሚውል 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸው ተገለጸ።
የምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
እስከ አሁን 313 ሺህ 260 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ የጫኑ ስድስት መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውንና ከዚህ ጭነት ውስጥ 256 ሺህ 398 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ገልጿል።
ቀሪው ማዳበሪያ በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኝም ነው የጠቆመው።

በተጨማሪም 56 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች ሰባተኛ መርከብ ትናንት ዶራሌ ሁለገብ ወደብ ደርሳ ጭነት በማራገፍ ላይ መሆኗንም አመልክቷል።
በሚቀጥሉት ቀናትም ተጨማሪ አራት አፈር ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጂቡቲ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቋል።

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026