
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የሞጆ ደረቅ ወደብ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን ገለፁ።
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 80 በመቶ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል።

የሞጆ ደረቅ ወደብን ወደ ሁለገብ የሎጅስቲክስ ማዕከል በመቀየር የወጪና ገቢ ንግድን ለማቀላጠፍ ከዓመታት በፊት የማስፋፊያ ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተወጣጡ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱ ተመልክተዋል።
የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፥ የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው።
በ60 ሄክታር ላይ በሚከናወነው የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የመሠረተ ልማት፣ የኮንክሪት ንጣፍ፣ የአይሲቲ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል፣ የአጥርና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሥራ 80 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፥ ፕሮጀክቱ በቀጣይ ዓመት ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የወደቡን የማስተናገድ አቅም፣ ቅልጥፍና እና ተዛማጅ የሎጂስቲክስ አገልግሎቶች ደረጃ ከመሰረቱ ይቀይራልም ብለዋል።

የፕሮጀክቱ ሳይት ኢንጂነር ሊና ኑሩ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አሁን ላይ መሰረታዊ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ የማጠናቀቂያ ስራዎች ለመስራት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የኢትዮ-ጂቡቲን የንግድ ኮሪደር አቅም ታሳቢ በማድረግና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሸከም ታስቦ ነው እየተገነባ ያለው።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026