አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የሞጆ ደረቅ ወደብ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን ገለፁ።
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 80 በመቶ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል።
የሞጆ ደረቅ ወደብን ወደ ሁለገብ የሎጅስቲክስ ማዕከል በመቀየር የወጪና ገቢ ንግድን ለማቀላጠፍ ከዓመታት በፊት የማስፋፊያ ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተወጣጡ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱ ተመልክተዋል።
የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፥ የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው።
በ60 ሄክታር ላይ በሚከናወነው የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የመሠረተ ልማት፣ የኮንክሪት ንጣፍ፣ የአይሲቲ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል፣ የአጥርና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሥራ 80 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፥ ፕሮጀክቱ በቀጣይ ዓመት ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የወደቡን የማስተናገድ አቅም፣ ቅልጥፍና እና ተዛማጅ የሎጂስቲክስ አገልግሎቶች ደረጃ ከመሰረቱ ይቀይራልም ብለዋል።
የፕሮጀክቱ ሳይት ኢንጂነር ሊና ኑሩ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አሁን ላይ መሰረታዊ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ የማጠናቀቂያ ስራዎች ለመስራት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የኢትዮ-ጂቡቲን የንግድ ኮሪደር አቅም ታሳቢ በማድረግና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሸከም ታስቦ ነው እየተገነባ ያለው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025