
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የሞጆ ደረቅ ወደብ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን ገለፁ።
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 80 በመቶ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል።

የሞጆ ደረቅ ወደብን ወደ ሁለገብ የሎጅስቲክስ ማዕከል በመቀየር የወጪና ገቢ ንግድን ለማቀላጠፍ ከዓመታት በፊት የማስፋፊያ ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተወጣጡ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱ ተመልክተዋል።
የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፥ የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው።
በ60 ሄክታር ላይ በሚከናወነው የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የመሠረተ ልማት፣ የኮንክሪት ንጣፍ፣ የአይሲቲ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል፣ የአጥርና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሥራ 80 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፥ ፕሮጀክቱ በቀጣይ ዓመት ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የወደቡን የማስተናገድ አቅም፣ ቅልጥፍና እና ተዛማጅ የሎጂስቲክስ አገልግሎቶች ደረጃ ከመሰረቱ ይቀይራልም ብለዋል።

የፕሮጀክቱ ሳይት ኢንጂነር ሊና ኑሩ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አሁን ላይ መሰረታዊ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ የማጠናቀቂያ ስራዎች ለመስራት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የኢትዮ-ጂቡቲን የንግድ ኮሪደር አቅም ታሳቢ በማድረግና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሸከም ታስቦ ነው እየተገነባ ያለው።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026