አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚችል ስርዓተ-ምግብ ለመፍጠር የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ(ዶ/ር) ገለጹ።
ዋና ዳይሬክተሩ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የተለያዩ ስራዎች እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመንና የምግብ ዋስትና እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ የሚያጠናክር የሚኒስትሮች ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተለያዩ ስራዎችን እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ ኢትዮጵያ ግብርና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
በመስኖ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን የሚያፋጥኑ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እነዚህም መንግስት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመፍጠር ተግባራዊ ምላሽ መስጠቱን ዐቢይ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እና ኒዉትሪሽን አስተባባሪ ጌታቸው ድሪባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጋላጭነትን የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመን፣ ዓይነተ ብዙ ምግብ ለማምረት፣ በንጥረ ምግብ የበለጸጉ ምግቦችን ለማቅረብ የተጀመሩ ስራዎች የተሻለ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራ ኃላፊዎቹ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የበለጠ ለመቋቋም በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ ማጠናከርና የዘርፎችን ትስስር ማጎልበትም ሌላኛው ወሳኝ የቤት ሥራ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025