
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚችል ስርዓተ-ምግብ ለመፍጠር የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ(ዶ/ር) ገለጹ።
ዋና ዳይሬክተሩ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የተለያዩ ስራዎች እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመንና የምግብ ዋስትና እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ የሚያጠናክር የሚኒስትሮች ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተለያዩ ስራዎችን እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ ኢትዮጵያ ግብርና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
በመስኖ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን የሚያፋጥኑ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እነዚህም መንግስት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመፍጠር ተግባራዊ ምላሽ መስጠቱን ዐቢይ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እና ኒዉትሪሽን አስተባባሪ ጌታቸው ድሪባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጋላጭነትን የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመን፣ ዓይነተ ብዙ ምግብ ለማምረት፣ በንጥረ ምግብ የበለጸጉ ምግቦችን ለማቅረብ የተጀመሩ ስራዎች የተሻለ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራ ኃላፊዎቹ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የበለጠ ለመቋቋም በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ ማጠናከርና የዘርፎችን ትስስር ማጎልበትም ሌላኛው ወሳኝ የቤት ሥራ ነው ብለዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026