የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ተጽዕኖ ለመቋቋም በግብርናው ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች የስርዓተ-ምግብ ሽግግርን እያፋጠኑ ነው- ማንደፍሮ ንጉሤ(ዶ/ር)</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚችል ስርዓተ-ምግብ ለመፍጠር የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ(ዶ/ር) ገለጹ።

ዋና ዳይሬክተሩ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የተለያዩ ስራዎች እያከናወነች ትገኛለች።

በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመንና የምግብ ዋስትና እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ የሚያጠናክር የሚኒስትሮች ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተለያዩ ስራዎችን እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል።

ይህንን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ ኢትዮጵያ ግብርና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡

በመስኖ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን የሚያፋጥኑ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

እነዚህም መንግስት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመፍጠር ተግባራዊ ምላሽ መስጠቱን ዐቢይ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እና ኒዉትሪሽን አስተባባሪ ጌታቸው ድሪባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጋላጭነትን የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመን፣ ዓይነተ ብዙ ምግብ ለማምረት፣ በንጥረ ምግብ የበለጸጉ ምግቦችን ለማቅረብ የተጀመሩ ስራዎች የተሻለ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራ ኃላፊዎቹ አንስተዋል፡፡

በቀጣይም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የበለጠ ለመቋቋም በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ ማጠናከርና የዘርፎችን ትስስር ማጎልበትም ሌላኛው ወሳኝ የቤት ሥራ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026