
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚችል ስርዓተ-ምግብ ለመፍጠር የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ(ዶ/ር) ገለጹ።
ዋና ዳይሬክተሩ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የተለያዩ ስራዎች እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመንና የምግብ ዋስትና እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ የሚያጠናክር የሚኒስትሮች ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተለያዩ ስራዎችን እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ ኢትዮጵያ ግብርና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
በመስኖ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን የሚያፋጥኑ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እነዚህም መንግስት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመፍጠር ተግባራዊ ምላሽ መስጠቱን ዐቢይ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እና ኒዉትሪሽን አስተባባሪ ጌታቸው ድሪባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጋላጭነትን የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ግብርናውን ለማዘመን፣ ዓይነተ ብዙ ምግብ ለማምረት፣ በንጥረ ምግብ የበለጸጉ ምግቦችን ለማቅረብ የተጀመሩ ስራዎች የተሻለ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራ ኃላፊዎቹ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የበለጠ ለመቋቋም በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ ማጠናከርና የዘርፎችን ትስስር ማጎልበትም ሌላኛው ወሳኝ የቤት ሥራ ነው ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026